-
የፍርድ ቀን ምንድን ነው?ትክክለኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምንድን ነው?
-
-
ሐዋርያው ዮሐንስ የፍርድ ቀንን አስመልክቶ ራእይ 20:11, 12 ላይ የሰጠው መግለጫ እንዲህ ይላል:- “ታላቅ ነጭ ዙፋንና በእርሱም ላይ የተቀመጠውን አየሁ። ምድርና ሰማይ ከፊቱ ሸሹ፤ ስፍራም አልተገኘላቸውም። ሙታንን፣ ታላላቆችንና ታናናሾችን በዙፋኑ ፊት ቆመው አየሁ፤ መጻሕፍትም ተከፈቱ። ሌላም መጽሐፍ፣ እርሱም የሕይወት መጽሐፍ ተከፈተ፤ ሙታንም በመጻሕፍቱ ተጽፎ በተገኘው መሠረት እንደ ሥራቸው መጠን ተፈረደባቸው።” እዚህ ላይ የተገለጸው ፈራጅ ማን ነው?
-
-
የፍርድ ቀን ምንድን ነው?ትክክለኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ምንድን ነው?
-
-
በሺው ዓመት ጊዜ ውስጥ ኢየሱስ ክርስቶስ ‘በሕያዋንና በሙታን ላይ ይፈርዳል።’ (2 ጢሞቴዎስ 4:1) “ሕያዋን” የተባሉት ከአርማጌዶን የሚተርፉ “እጅግ ብዙ ሕዝብ” ናቸው። (ራእይ 7:9-17) ከዚህም በተጨማሪ ሐዋርያው ዮሐንስ ‘ሙታን በፍርድ ዙፋን ፊት ቆመው’ ተመልክቷል። ኢየሱስ ቃል በገባው መሠረት “መቃብር ውስጥ ያሉ ሁሉ” የክርስቶስን ድምፅ ሰምተው በትንሣኤ አማካኝነት ይነሣሉ። (ዮሐንስ 5:28, 29፤ የሐዋርያት ሥራ 24:15) ሆኖም ሁሉም የሚፈረድባቸው በምን መሠረት ነው?
ሐዋርያው ዮሐንስ ባየው ራእይ ላይ ‘መጻሕፍት የተከፈቱ’ ሲሆን ‘ሙታን በመጻሕፍቱ ተጽፎ በተገኘው መሠረት እንደ ሥራቸው መጠን ተፈርዶባቸዋል።’ እነዚህ መጻሕፍት ሰዎች ቀደም ሲል የፈጸሟቸው ድርጊቶች የተመዘገቡባቸው ናቸው? አይደሉም፤ ፍርዱ የሚሰጠው ሰዎች ቀደም ሲል በፈጸሟቸው ድርጊቶች ላይ ተመርኩዞ አይደለም። ይህን እንዴት እናውቃለን? መጽሐፍ ቅዱስ “የሞተ ከኀጢአት ነጻ ወጥቶአል” ይላል። (ሮሜ 6:7) ስለዚህ እነዚህ ሰዎች ከሞት የሚነሱት የቀድሞ ኃጢአታቸው ተሽሮላቸው ነው። በመሆኑም መጻሕፍቱ አምላክ ወደፊት የሚያወጣቸውን መሥፈርቶች የሚያመለክቱ መሆን አለባቸው። ከአርማጌዶን የሚተርፉትም ሆኑ ከሞት የሚነሱት ሰዎች ለዘላለም መኖር እንዲችሉ ይሖዋ በሺው ዓመት ወቅት ሊያወጣቸው የሚችላቸውን መሥፈርቶች ጨምሮ ሁሉንም የአምላክ ትእዛዛት ማክበር ያስፈልጋቸዋል። ስለዚህ ሰዎች ፍርድ የሚሰጣቸው በፍርድ ቀን የሚፈጽሙትን ድርጊት መሠረት በማድረግ ነው።
-