-
የእሳት ሐይቅ ምንድን ነው? ገሃነም ነው? ወይስ ሲኦል?የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
-
-
ዘላለማዊ ጥፋትን ያመለክታል
መጽሐፍ ቅዱስ፣ ስለ እሳት ሐይቅ ሲናገር “ሁለተኛው ሞት ማለት ነው” ይላል። (ራእይ 20:14፤ 21:8) በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተገለጸው የመጀመሪያው ሞት በአዳም ኃጢአት ምክንያት የመጣው ሞት ነው። በአዳም ኃጢአት ምክንያት የሞቱ ሰዎች በትንሣኤ አማካኝነት እንደገና ሕይወት ማግኘት ይችላሉ፤ ደግሞም ወደፊት አምላክ ሞትን ያስወግደዋል።—1 ቆሮንቶስ 15:21, 22, 26
ምሳሌያዊ ትርጉም ካለው የእሳት ሐይቅ መውጣት የሚቻልበት መንገድ የለም
የእሳት ሐይቅ ግን ከዚህ የሚለይ ሲሆን ሁለተኛውን ሞት ያመለክታል። ይህ ዓይነቱ ሞትም ሙሉ በሙሉ ከሕልውና ውጭ መሆን ማለት ነው፤ ይሁን እንጂ ለሁለተኛው ሞት ትንሣኤ እንደሚኖር መጽሐፍ ቅዱስ አይገልጽም። ለምሳሌ ያህል፣ ኢየሱስ “የሞትና የሲኦል መክፈቻ” እንዳለው መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል፤ ይህም ኢየሱስ በአዳም ኃጢአት ምክንያት የሞቱ ሰዎችን ከሞት እስራት የማስለቀቅ ሥልጣን እንዳለው የሚያሳይ ነው። (ራእይ 1:18፤ 20:13 አ.መ.ት) ይሁንና የእሳት ሐይቅ መክፈቻ ለኢየሱስም ሆነ ለማንም አልተሰጠም። ይህ ምሳሌያዊ ሐይቅ፣ ዘላለማዊ ቅጣትን ይኸውም ለዘለቄታው መጥፋትን የሚያመለክት ነው።—2 ተሰሎንቄ 1:9
-