-
መጽሐፍ ቅዱስ የተስፋ ብርሃን ይፈነጥቃልለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
-
-
2. መጽሐፍ ቅዱስ ወደፊት ምን ዓይነት ጊዜ እንደሚመጣ ይናገራል?
መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ወደፊቱ ጊዜ ሲናገር “ከእንግዲህ ወዲህ ሞት አይኖርም፤ ሐዘንም ሆነ ጩኸት እንዲሁም ሥቃይ ከእንግዲህ ወዲህ አይኖርም” ይላል። (ራእይ 21:4ን አንብብ።) እንደ ድህነት፣ የፍትሕ መጓደል፣ ሕመምና ሞት ያሉ በዛሬው ጊዜ ሕይወት ተስፋ አስቆራጭ እንዲሆንብን ያደረጉ ችግሮች ይወገዳሉ። መጽሐፍ ቅዱስ ሰዎች ገነት በምትሆነው ምድር ላይ ለዘላለም በደስታ እንደሚኖሩ ይገልጻል።
-
-
ሰዎች ችግርና መከራ የሚደርስባቸው ለምንድን ነው?ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
-
-
7. አምላክ በሰዎች ላይ የሚደርሰውን መከራ በሙሉ ያስወግዳል
ኢሳይያስ 65:17ን እና ራእይ 21:3, 4ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ተወያዩ፦
ይሖዋ በሰው ልጆች ላይ የደረሱት መጥፎ ነገሮች ያስከተሉትን ጉዳት ሙሉ በሙሉ እንደሚያስተካክል ማወቅህ የሚያጽናናህ ለምንድን ነው?
ይህን ታውቅ ነበር?
ሰይጣን የመጀመሪያውን ውሸት ሲናገር የይሖዋን ስም አጥፍቷል። ይሖዋ ፍትሐዊና አፍቃሪ ገዢ እንዳልሆነ የሚያስመስል ሐሳብ በመሰንዘር ስሙን አጉድፏል። በቅርቡ ይሖዋ በሰው ልጆች ላይ የደረሰውን ጉዳት ሙሉ በሙሉ በማስተካከል መልካም ስሙን ያድሳል። በሌላ አባባል የእሱ አገዛዝ ከሁሉ የተሻለ እንደሆነ ያሳያል። የይሖዋ ስም መቀደስ ወይም ከነቀፋ ነፃ መሆን በጽንፈ ዓለም ውስጥ ተቀዳሚ ቦታ የሚሰጠው ጉዳይ ነው።—ማቴዎስ 6:9, 10
-