-
“ያለህን አጽንተህ ያዝ”ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
17 በ1918 የዮሐንስ ክፍል አባሎች የሆኑት ቅቡዓን ክርስቲያኖች በፊልድልፍያ እንደ ነበረው ጠንካራ ጉባኤ ከዘመናዊው “የሰይጣን ምኩራብ” የሚደርስባቸውን ተቃውሞ መቋቋም ነበረባቸው። መንፈሳዊ አይሁዳውያን ነን ይሉ የነበሩት የሕዝበ ክርስትና ሃይማኖታዊ መሪዎች ገዥዎችን በማሳሳትና በመጠምዘዝ እውነተኛ ክርስቲያኖችን ለማፈን መሣሪያ አድርገው ተጠቀሙባቸው። ይሁን እንጂ እነዚህ ክርስቲያኖች የኢየሱስን የጽናት ቃል ጠብቀው ለመኖር ብርቱ ጥረት አድርገዋል። ስለዚህ በተሰጣቸው መንፈሳዊ እርዳታ ያላቸውን ‘ትንሽ ኃይል’ ጠብቀው ስለተገኙ ተከፍቶ ይጠብቃቸው በነበረው በር ለመግባት ተነሳሱ። ግን ወደዚህ በር የገቡት እንዴት ነው?
-
-
“ያለህን አጽንተህ ያዝ”ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
19. የዮሐንስ ክፍል ኢየሱስ በ1919 የሰጠውን ኃላፊነት የተወጣው እንዴት ነው? ምንስ ውጤት አስገኘ?
19 ቅቡዓን ቀሪዎች ከ1919 ጀምሮ የኢየሱስን ምሳሌ በመከተል የመንግሥቱን ምሥራች የማወጅ ዘመቻ ጀምረዋል። (ማቴዎስ 4:17፤ ሮሜ 10:18) በዚህም ዘመቻቸው ምክንያት ዘመናዊ የሰይጣን ምኩራብ ከሆነችው ከሕዝበ ክርስትና ውስጥ የወጡ አንዳንድ ሰዎች ንስሐ ገብተው በመስገድ ለባሪያው የተሰጠውን ሥልጣን ተቀብለዋል። እነዚህም ሰዎች ቀደም ካሉት የዮሐንስ ክፍል አባሎች ጋር በመተባበር ይሖዋን ማገልገል ጀምረዋል። ይህ ሥራ የኢየሱስ ቅቡዓን ወንድሞች ቁጥር እስከ ሞላበት ጊዜ ድረስ ቀጥሎአል። ከዚያም በኋላ ‘ከአሕዛብ ሁሉ የተውጣጡ እጅግ ብዙ ሰዎች’ ለቅቡዓን ባሮች መስገድ ጀምረዋል። (ራእይ 7:3, 4, 9) ባሪያውና እነዚህ እጅግ ብዙ ሰዎች የይሖዋ ምሥክሮች በመሆን አንድ መንጋ ሆነው ያገለግላሉ።
-