-
በጌታ ቀን የደረሰ ልዩ ልዩ የምድር መናወጥራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
17. ታላቁ የምድር መናወጥ ፀሐይን፣ ጨረቃንና ከዋክብትን የሚነካው እንዴት ነው?
17 ዮሐንስ ቀጥሎ እንደሚገልጽልን የምድር መናወጡ በሰማያት ላይ እንኳን ውጤት በአስከተሉ አስደንጋጭ ሁኔታዎች ታጅቦአል። እንዲህ ይላል:- “ፀሐይም እንደ ማቅ ጠጉር ጥቁር ሆነ፣ ጨረቃም በሞላው እንደ ደም ሆነ፣ በለስም በብርቱ ነፋስ ተናውጣ ቃርያዋን ፍሬ እንደምትጥል የሰማይ ከዋክብት ወደ ምድር ወደቁ።” (ራእይ 6:12ለ, 13) በጣም የሚያስፈራ ሁኔታ ነው። ይህ ትንቢት ቃል በቃል የሚፈጸም ቢሆን ምን ያህል አስፈሪና አስደንጋጭ ጨለማ እንደሚፈጠር ልትገምቱ ትችላላችሁ። በቀን ሙቀት የሚሰጥና ሰውነት የሚያዝናና የፀሐይ ብርሃን አይኖርም። በሌሊት ደግሞ ልብ የሚያረጋጋ ብርማ ቀለም የጨረቃ ብርሃን አይኖርም። በጠራው ሰማይ ላይ ይንቆጠቆጡ የነበሩት እልፍ አእላፍ ከዋክብት አይታዩም። በእነዚህ ሁሉ ፋንታ ቀዝቃዛ የሆነና ጥቅጥቅ ያለ አስፈሪ ጨለማ ይኖራል።—ከማቴዎስ 24:29 ጋር አወዳድር።
-
-
በጌታ ቀን የደረሰ ልዩ ልዩ የምድር መናወጥራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
17. ታላቁ የምድር መናወጥ ፀሐይን፣ ጨረቃንና ከዋክብትን የሚነካው እንዴት ነው?
17 ዮሐንስ ቀጥሎ እንደሚገልጽልን የምድር መናወጡ በሰማያት ላይ እንኳን ውጤት በአስከተሉ አስደንጋጭ ሁኔታዎች ታጅቦአል። እንዲህ ይላል:- “ፀሐይም እንደ ማቅ ጠጉር ጥቁር ሆነ፣ ጨረቃም በሞላው እንደ ደም ሆነ፣ በለስም በብርቱ ነፋስ ተናውጣ ቃርያዋን ፍሬ እንደምትጥል የሰማይ ከዋክብት ወደ ምድር ወደቁ።” (ራእይ 6:12ለ, 13) በጣም የሚያስፈራ ሁኔታ ነው። ይህ ትንቢት ቃል በቃል የሚፈጸም ቢሆን ምን ያህል አስፈሪና አስደንጋጭ ጨለማ እንደሚፈጠር ልትገምቱ ትችላላችሁ። በቀን ሙቀት የሚሰጥና ሰውነት የሚያዝናና የፀሐይ ብርሃን አይኖርም። በሌሊት ደግሞ ልብ የሚያረጋጋ ብርማ ቀለም የጨረቃ ብርሃን አይኖርም። በጠራው ሰማይ ላይ ይንቆጠቆጡ የነበሩት እልፍ አእላፍ ከዋክብት አይታዩም። በእነዚህ ሁሉ ፋንታ ቀዝቃዛ የሆነና ጥቅጥቅ ያለ አስፈሪ ጨለማ ይኖራል።—ከማቴዎስ 24:29 ጋር አወዳድር።
-
-
በጌታ ቀን የደረሰ ልዩ ልዩ የምድር መናወጥራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
20. ታላቁ የምድር መናወጥ ሲጀምር በዚህ ሥርዓት ላይ ምን ዓይነት አስፈሪ ሁኔታ ይፈጸማል?
20 ታላቁ የምድር መናወጥ ምድርን መምታት በሚጀምርበት ጊዜ ደግሞ በተመሳሳይ ሁኔታ ይህ መላው የዓለም ሥርዓት በፍርሐትና በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ይዋጣል። የሰይጣን ምድራዊ ሥርዓት ደማቅ ብርሃን ሰጪዎች ምንም ዓይነት የተስፋ ብርሃን መፈንጠቅ ያቅታቸዋል። በዛሬው ጊዜ እንኳን የምድር ፖለቲካዊ መሪዎች፣ በተለይ በሕዝበ ክርስትና አገሮች ውስጥ የሚገኙት መሪዎች በምግባረ ብልሹነታቸው፣ በውሸታምነታቸው፣ በጉቦኛነታቸው በጣም የታወቁ ሆነዋል። (ኢሳይያስ 28:14-19) ፈጽሞ ሊታመኑ በማይችሉበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል። ሲፈነጥቁ የቆዩት የብርሃን ጭላንጭል ይሖዋ የቅጣት ፍርዱን በሚያስፈጽምበት ጊዜ ፈጽሞ ይዳፈናል። በምድር ጉዳዮች ላይ የነበራቸው ጨረቃ መሰል ተጽእኖ ሞት የሚያስከትልና በደም የተበከለ መሆኑ ይጋለጣል። እንደ ከዋክብት የሚታዩት ዓለማዊ ዝነኞቻቸው ተቃጥለው እንደሚጠፉ ተወርዋሪ ኮከቦችና በአውሎ ነፋስ ተበታትኖ እንደሚረግፍ ያልበሰለ ፍሬ ይሆናሉ። መላው ምድራችን ‘ከዓለም መጀመሪያ ጀምሮ ሆኖ በማያውቅና ከእንግዲህ ወዲያም በማይሆን ታላቅ መከራ’ ይናወጣል። (ማቴዎስ 24:21) ምንኛ የሚያስፈራ ሁኔታ ነው!
-