-
እጅግ ብዙ ሰዎችራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
17. (ሀ) ከ24ቱ ሽማግሌዎች አንዱ ምን ዓይነት ጥያቄ አነሳ? ሽማግሌው መልሱን ለማግኘት መቻሉ ምን ያመለክታል? (ለ) የሽማግሌው ጥያቄ ምላሽ ያገኘው መቼ ነበር?
17 ከሐዋርያው ዮሐንስ ዘመን ጀምሮ እስከ ጌታ ቀን ድረስ ቅቡዓን ክርስቲያኖች ስለ እጅግ ብዙ ሰዎች ማንነት ግራ ተጋብተው ነበር። ስለዚህ ከ24ቱ ሽማግሌዎች አንዱ የሚከተለውን ተገቢ ጥያቄ በመጠየቅ የዮሐንስን አሳብ መቀስቀሱ ተገቢ ነው። “ከሽማግሌዎቹም አንዱ ተመልሶ:- እነዚህ ነጩን ልብስ የለበሱ እነማን ናቸው? ከወዴትስ መጡ? አለኝ። እኔም:- ጌታ ሆይ አንተ ታውቃለህ አልሁት።” (ራእይ 7:13, 14ሀ) አዎ፣ ይህ ሽማግሌ መልሱን ሊያገኝና ለዮሐንስ ሊነግረው ይችላል። ይህም ከሙታን የተነሱት የ24ቱ ሽማግሌዎች አባላት በዘመናችን መለኮታዊውን እውነት በማስተላለፍ ሥራ እንደሚካፈሉ ያመለክታል። በምድር ያሉት የዮሐንስ ክፍል አባሎችም ቢሆኑ የእጅግ ብዙ ሰዎችን ማንነት ሊያውቁ የቻሉት ይሖዋ በመካከላቸው የሚሠራውን ሥራ በመመልከት ነው። ይሖዋ የወሰነው ጊዜ ሲደርስ በ1935 መለኮታዊው ብርሃን በቲኦክራቲካዊው ሰማይ ላይ ብሩሕ ሆኖ እንደፈነጠቀ ወዲያውኑ ተገነዘቡ።
-
-
እጅግ ብዙ ሰዎችራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
22. ዮሐንስ ስለ እጅግ ብዙ ሰዎች ምን ተጨማሪ መረጃ አግኝቶ ነበር?
22 ዮሐንስ በመለኮታዊው የመልእክት ማስተላለፊያ መስመር በኩል ስለዚህ እጅግ ብዙ ሰዎች ተጨማሪ መረጃ አግኝቶአል። “አለኝም [ሽማግሌው]:- እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው። ልብሳቸውንም አጥበው በበጉ ደም አነጹ። ስለዚህ በእግዚአብሔር ዙፋን ፊት አሉ፣ ሌሊትና ቀንም በመቅደሱ ያመልኩታል፣ በዙፋኑም ላይ የተቀመጠው በእነርሱ ላይ ያድርባቸዋል።” —ራእይ 7:14ለ, 15
23. እጅግ ብዙ ሰዎች ‘የወጡበት’ ታላቅ መከራ ምንድን ነው?
23 ቀደም ባለው ጊዜ ኢየሱስ በመንግሥት ክብር የሚገኝበት ጊዜ ሲፈጸም “ከዓለም መጀመሪያ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ያልሆነ እንግዲህም ከቶ የማይሆን ታላቅ መከራ” እንደሚሆን ተናግሮ ነበር። (ማቴዎስ 24:21, 22) በዚህ ትንቢት ፍፃሜ መሠረት መላእክቱ መላውን የሰይጣን ዓለማዊ ሥርዓት ለማጥፋት አራቱን የምድር ነፋሳት ይለቃሉ። በመጀመሪያ የምትጠፋው የሐሰት ሃይማኖት ግዛት የሆነችው ታላቂቱ ባቢሎን ነች። ከዚያም በኋላ በመከራው ፍጻሜ ላይ ኢየሱስ ከ144, 000ዎቹ ክፍል በምድር ላይ የቀሩትንና እጅግ ብዙ ሰዎችን ነጻ ያወጣቸዋል።—ራእይ 7:1፤ 18:2
24. የእጅግ ብዙ ሰዎች አባሎች የሆኑ ግለሰቦች ለመዳን ብቃት የሚያገኙት እንዴት ነው?
24 የእጅግ ብዙ ሰዎች ግለሰብ አባሎች ለመዳን የሚያስችላቸውን ብቃት የሚያገኙት እንዴት ነው? ሽማግሌው “ልብሳቸውን በበጉ ደም አጥበው” እንዳነጹ ለዮሐንስ ነግሮታል። በሌላ አነጋገር ኢየሱስ ቤዛቸው መሆኑን አምነዋል፣ ሕይወታቸውን ለይሖዋ ወስነዋል፣ ውሳኔያቸውንም በውኃ ጥምቀት አሳይተዋል፣ በጥሩ ሥነ ምግባር በመመላለስም “በጎ ሕሊና” ይዘዋል። (1 ጴጥሮስ 3:16, 21፤ ማቴዎስ 20:28) ስለዚህ በይሖዋ ፊት ንጹሐንና ጻድቃን ናቸው። ራሳቸውንም “ከዓለም እድፍ” ጠብቀው ይኖራሉ።—ያዕቆብ 1:27
-