-
ዮሐንስ ክብር የተቀዳጀውን ኢየሱስን ተመለከተራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
5. (ሀ) አንድ ድምፅ ዮሐንስን ምን እንዲያደርግ ጠየቀው? (ለ) የሰባቱ ጉባኤዎች አቀማመጥ የመጽሐፍ ጥቅልል ለመላክ አመቺ የነበረው ለምንድን ነው?
5 በዚህ የመጀመሪያ ራእይ ዮሐንስ ምንም ነገር ከማየቱ በፊት አንድ ነገር ይሰማል። “በኋላዬም የመለከትን ድምፅ የሚመስል ታላቅ ድምፅ ሰማሁ፣ እንዲሁም:- የምታየውን በመጽሐፍ ጽፈህ ወደ ኤፌሶንና ወደ ሰምርኔስ ወደ ጴርጋሞንም ወደ ትያጥሮንም ወደ ሰርዴስም ወደ ፊልድልፍያም ወደ ሎዶቅያም በእስያ ወዳሉት ወደ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት ላክ አለኝ።” (ራእይ 1:10ለ, 11) እንደ መለከት ጩኸት ያለ ኃይልና የማዘዝ ሥልጣን የነበረው ድምፅ ዮሐንስን ለሰባቱ ጉባኤዎች እንዲጽፍ አዘዘው። ዮሐንስ ተከታታይ መልእክቶችን መቀበልና የሚያየውንና የሚሰማውን ለሌሎች ማስተላለፍ ነበረበት። እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት ጉባኤዎች በዮሐንስ ዘመን በትክክል የነበሩ ጉባኤዎች እንደሆኑ እናስተውል። ሁሉም ከጳጥሞስ በስተማዶ ከባሕር ባሻገር በታናሽቱ እስያ የሚገኙ ጉባኤዎች ነበሩ። በአካባቢው በነበረው ግሩም የሆነ የሮማውያን አውራ ጎዳና አማካኝነት ከአንዱ ጉባኤ ወደሌላው ጉባኤ በቀላሉ መጓዝ ይቻል ነበር። አንድ መልእክተኛ የመጽሐፉን ጥቅልል ተሸክሞ ከአንድ ጉባኤ ወደሌላው ለማድረስ ምንም አይቸገርም። እነዚህ ሰባት ጉባኤዎች በዘመናችን በአንድ የይሖዋ ምስክሮች ክልል ውስጥ በሚገኝ አንድ አካባቢ ሊመሰሉ ይችላሉ።
-
-
ዮሐንስ ክብር የተቀዳጀውን ኢየሱስን ተመለከተራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
[በገጽ 23 ላይ የሚገኙ ሥዕሎች]
ሰባቱ ጉባኤዎች በነበሩባቸው ከተሞች የተደረገው የመሬት ቁፋሮ ጥናት የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገብ ትክክል መሆኑን አረጋግጦአል። በዛሬው ጊዜ በመላው ዓለም ያሉትን ጉባኤዎች የሚቀሰቅሱትን የኢየሱስ አበረታች መልእክቶች የመጀመሪያው መቶ ዘመን ክርስቲያኖች የተቀበሉት በእነዚህ ቦታዎች ሆነው ነበር
ጴርጋሞን
ሰምርኔስ
ትያጥሮን
ሰርዴስ
ኤፌሶን
ፊልድልፍያ
ሎዶቂያ
-