-
እጅግ ብዙ ሰዎችራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
26. እጅግ ብዙ ሰዎች ምን ሌላ በረከቶች ያገኛሉ?
26 ሽማግሌው እንደሚከተለው በማለት ይቀጥላል:- “ከእንግዲህ ወዲህ አይራቡም፣ ከእንግዲህም ወዲህ አይጠሙም፣ ፀሐይም ትኩሳትም ሁሉ ከቶ አይወርድባቸውም በዙፋኑ መካከል ያለው በጉ እረኛቸው ይሆናልና፣ ወደ ሕይወትም ውኃ ምንጭ ይመራቸዋልና፣ እግዚአብሔርም እንባዎችን ሁሉ ከዓይናቸው ያብሳል።” (ራእይ 7:16, 17) አዎ፣ በእርግጥም ይሖዋ ጥሩ አስተናጋጅ ነው። ይሁን እንጂ እነዚህ ቃላት ምን የጠለቀ ትርጉም አላቸው?
-
-
እጅግ ብዙ ሰዎችራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
29 አንተም ከእነዚህ እጅግ ብዙ ሰዎች አንዱ ከሆንክ የዚህ የሰይጣን ሥርዓት ቀን እየጨለመ በሄደበት በዚህ ዘመን ምንም ዓይነት ችግርና ተጽዕኖ ቢደርስብህም ያለህ ጥሩ የልብ ሁኔታ ‘በደስታ እልል ለማለት’ ይገፋፋሃል። (ኢሳይያስ 65:14) በዚህ ረገድ አሁንም እንኳን ቢሆን ይሖዋ ‘ከዓይኖችህ እንባን ሁሉ ሊጠርግልህ’ ይችላል። ከእንግዲህ ወዲያ በጣም የሚያተኩሰው የአምላክ የቁጣ ፍርድ “ፀሐይ” አያስፈራህም። አራቱ የጥፋት ነፋሳት በሚለቀቁበት ጊዜም ከሚያተኩሰው የይሖዋ ቁጣ ትድናለህ። ከዚህ ጥፋት በኋላ በጉ ሕይወት ወደሚያድሰው “የሕይወት ውኃ ምንጭ” ይመራሃል። ይህም ውኃ ይሖዋ የዘላለም ሕይወት እንድታገኝ ያዘጋጀውን ዝግጅት በሙሉ ያመለክታል። ቀስ በቀስ ወደ ሰብዓዊ ፍጽምና ስለምትደርስ በበጉ ደም ያለህ እምነት ይረጋገጣል። እናንተ የእጅግ ብዙ ሰዎች አባሎች፣ ሞትን ከማይቀምሱት በሚልዮን የሚቆጠሩ ሰዎች መካከል ስለምትሆኑ በዓይነቱ ልዩ የሆነ መብት ታገኛላችሁ። በእርግጥም ከዓይናችሁ እንባ ሁሉ ይጠረጋል።—ራእይ 21:4
-