-
የመጀመሪያው ወዮታ፣ አንበጦችራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
9. አንበጦቹ ምን የውጊያ መመሪያ ተሰጥቶአቸዋል?
9 እነዚህ አንበጦች የተሰጣቸው የጦርነት መመሪያ ምን ነበር? ዮሐንስ ይነግረናል። “የእግዚአብሔር ማኅተም በግምባራቸው ከሌለባቸው ሰዎች በቀር በምድር ያለውን ሣር ቢሆን ወይም ማናቸውንም የለመለመ ነገር ወይም ማናቸውንም ዛፍ እንዳይጎዱ ተባለላቸው። አምስትም ወር ሊሣቅዩአቸው ተሰጣቸው እንጂ ሊገድሉአቸው አይደለም። እነርሱም የሚሣቅዩት ሥቃይ ጊንጥ ሰውን ነድፎ እንደሚሣቅይ ነው። በዚያም ወራት ሰዎች ሞትን ይፈልጋሉ፣ አያገኙትምም። ሊሞቱም ይመኛሉ ሞትም ከእነርሱ ይሸሻል።”—ራእይ 9:4-6
-
-
የመጀመሪያው ወዮታ፣ አንበጦችራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
11. (ሀ) አንበጦቹ የአምላክን ጠላቶች ለምን ያህል ጊዜ እንዲጎዱ ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል? ይህስ አጭር ጊዜ ያልሆነው ለምንድን ነው? (ለ) ሥቃዩ ምን ያህል ከባድ ነው?
11 ሥቃዩ የሚቆየው ለአምስት ወራት ነው። ታዲያ ይህ አጭር ጊዜ አይደለምን? ቃል በቃል ለአንበጣ አጭር ጊዜ አይደለም። አምስት ወር የአንድ አንበጣ አማካይ ዕድሜ ነው። ስለዚህ ዘመናዊዎቹ አንበጦች የአምላክን ጠላቶች የሚነድፉት በሕይወት በሚኖሩበት ጊዜ ሁሉ ነው። ከዚህም በላይ ሥቃዩ በጣም ከባድ ስለሆነ ሰዎች ሞትን እስከመምረጥ ይደርሳሉ። እውነት ነው፣ አንበጦቹ ከነደፉአቸው ሰዎች መካከል ራሳቸውን ለመግደል የሞከሩ እንዳሉ የሚያረጋገጥ ማስረጃ የለንም። ቢሆንም የአነጋገሩ ዘይቤ እንደ ጊንጥ ንክሻ የሚያሳምመው ሥቃይ ምን ያህል ከባድ እንደሆነ እንድንረዳ ያስችለናል። ይህም ሁኔታ ኤርምያስ አስቀድሞ ከተመለከተው ባቢሎናውያን ወራሪዎች በሚበታትኑአቸው ከሃዲ እሥራኤላውያን ላይ ካደረሱት ሥቃይ ጋር የሚመሳሰል ነው። እነዚህ እስራኤላውያን ከመኖር ሞትን መርጠው ነበር።—ኤርምያስ 8:3፤ በተጨማሪም መክብብ 4:2, 3ን ተመልከት።
-