-
ሁለቱን ምሥክሮች እንደገና ሕያው ማድረግራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
19. የራእይ መጽሐፍ በሚሰጠው መግለጫ መሠረት ሁለቱ ምሥክሮች የምሥክርነት ሥራቸውን ሲፈጽሙ ምን ይሆናል?
19 ይህ በሕዝበ ክርስትና ላይ የወረደው መቅሰፍት በጣም ከባድ ስለነበረ ሁለቱ ምሥክሮች ለ42 ወራት ማቅ ለብሰው ከመሰከሩ በኋላ ሕዝበ ክርስትና ባላት ዓለማዊ ተደማጭነት ተጠቅማ ‘አስገደለቻቸው።’ ዮሐንስ እንዲህ ሲል ጽፎአል:- “ምስክራቸውን ከፈጸሙ በኋላ ከጥልቁ የሚወጣው አውሬ ይዋጋቸዋል ያሸንፋቸውማል ይገድላቸውማል። በድናቸውም በታላቂቱ ከተማ አደባባይ ይተኛል እርስዋም በመንፈሳዊ ምሳሌ ሰዶምና ግብጽ የተባለች ደግሞ ጌታቸው የተሰቀለባት ናት። ከወገኖችና ከነገዶችም ከቋንቋዎችም ከአሕዛብም የሆኑ ሰዎች ሦስት ቀን ተኩል በድናቸውን ይመለከታሉ፣ በድናቸውም ወደ መቃብር ሊገባ አይፈቅዱም። እነዚህም ሁለት ነቢያት በምድር የሚኖሩትን ስለ ሣቀዩ በምድር የሚኖሩት በእነርሱ ላይ ደስ ይላቸዋል በደስታም ይኖራሉ እርስ በርሳቸውም ስጦታ ይሰጣጣሉ።”— ራእይ 11:7-10
-
-
ሁለቱን ምሥክሮች እንደገና ሕያው ማድረግራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
[በገጽ 168 ላይ የሚገኝ ሣጥን]
የራእይ 11:10 ደስታ
ሬይ ኤች አብራምስ በ1933 በታተመ ሰባኪያን የጦር መሣሪያ ሲያቀርቡ በተባለው መጽሐፋቸው ቀሳውስት ያለቀለት ምሥጢር የተባለውን በመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች የተዘጋጀ መጽሐፍ ምን ያህል አምርረው እንደተቃወሙ ገልጸዋል። ቀሳውስት የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎችንና የእነርሱን “ቸነፈራዊ ትምህርት” ለማስወገድ እንዴት እንደጣሩ አብራርተዋል። በዚህም ምክንያት ለጄ ኤፍ ራዘርፎርድና ለሰባት ባልንጀሮቹ የረዥም ዓመት የእስራት ፍርድ ምክንያት የሆነው ክስ ተመሠረተ። ዶክተር አብራምስ “ጉዳዩን ጠለቅ ብለን ስንመረምር ራስላውያንን ፈጽሞ ለመደምሰስ በተደረገው ጥረት የአብያተ ክርስቲያናትና የቀሳውስት እጅ እንዳለበት ለመረዳት እንችላለን። በካናዳ አገር በየካቲት ወር 1918 ቀሳውስት በእነዚህ ሰዎችና በጽሑፎቻቸው ላይ በተለይም ያለቀለት ምሥጢር በተባለው መጽሐፍ ላይ የተቀናጀ ዘመቻ ማካሄድ ጀመሩ። የዊኒፔግ ትሪቢዩን እንዳለው . . . መጽሐፋቸው ሊታገድ የቻለው በቀሳውስት ተጽእኖ ምክንያት እንደሆነ ይታመናል።”
ዶክተር አብራምስ እንዲህ በማለት ይቀጥላሉ:- “የሃያው ዓመት የእስራት ፍርድ የመወሰኑ ዜና ለሃይማኖታዊ ጋዜጦች አዘጋጆች በደረሰ ጊዜ ሁሉም ከትልቅ እስከ ትንሽ ድረስ በጣም ተደሰቱ። በየትኛውም የሃይማኖት ጽሑፍ የሐዘኔታ ቃል ለማግኘት አልቻልኩም። አፕቶን ሲንክልየር እንዳለው ‘ለስደቱ መነሳት በከፊል ምክንያት የሆነው የታወቁት ሃይማኖታዊ ድርጅቶች ጥላቻ እንደነበረ አያጠራጥርም።’ አብያተ ክርስቲያናት በቅንጅት ያደረጉት ጥረት መፈጸም ያልቻለውን አሁን መንግሥት ሊፈጽምላቸው የቻለ መሰለ።” ጸሐፊው የብዙ ሃይማኖታዊ ጽሑፎችን የነቀፌታ ቃላት ከጠቀሱ በኋላ ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት ቀድሞ የተሰጠውን ፍርድ መሻሩን ጠቀሱና “አብያተ ክርስቲያናት ውሳኔውን በዝምታ ተቀበሉት” ብለዋል።
-