-
የአንባቢያን ጥያቄዎችመጠበቂያ ግንብ—2014 | ኅዳር 15
-
-
እነዚህ ቅቡዓን ማቅ ለብሰው የሚሰብኩበት ጊዜ ሲያበቃ በአንጻራዊ ሁኔታ ለአጭር ጊዜ፣ ማለትም ለሦስት ቀን ተኩል እስር ቤት መግባታቸው በምሳሌያዊ ሁኔታ እንደተገደሉ ያሳያል። በአምላክ ሕዝብ ጠላቶች ዓይን ሲታይ የቅቡዓኑ ሥራ የሞተ ያህል ስለሆነ ለተቃዋሚዎች ታላቅ ደስታ አምጥቶላቸዋል።—ራእይ 11:8-10
ይሁን እንጂ ልክ በትንቢት በተነገረው መሠረት ሦስት ቀን ተኩሉ ሲያበቃ ሁለቱ ምሥክሮች ወደ ሕልውና ተመልሰዋል። እነዚህ ቅቡዓን ከእስር የተፈቱ ከመሆኑም በላይ ታማኝነታቸውን ለጠበቁት ቅቡዓን፣ አምላክ በጌታቸው በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ልዩ ሹመት ሰጥቷቸዋል። በእነዚህ የመጨረሻ ቀናት የአምላክን ሕዝቦች መንፈሳዊ ፍላጎት እንዲያሟሉ ሲባል ከእነዚህ ቅቡዓን መካከል የተወሰኑት በ1919 “ታማኝና ልባም ባሪያ” ሆነው ተሹመዋል።—ማቴ. 24:45-47፤ ራእይ 11:11, 12
-