-
ሁለቱን ምሥክሮች እንደገና ሕያው ማድረግራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
23. (ሀ) ከሦስት ቀን ተኩል በኋላ ሁለቱ ምሥክሮች ምን ሆኑ? ይህስ ጠላቶቻቸው ምን እንዲሰማቸው አደረገ? (ለ) ራእይ 11:11, 12 እና ይሖዋ በሸለቆ ውስጥ በነበሩት ደረቅ አጥንቶች ላይ እፍ ስለ ማለቱ የሚናገረው የሕዝቅኤል ትንቢት ዘመናዊ ፍጻሜያቸውን ያገኙት መቼ ነው?
23 ታላላቅ ጋዜጦችም የአምላክን ሕዝቦች በመንቀፍ ከቀሳውስት ጋር ተባብረዋል። አንድ ጋዜጣ “ያለቀለት ምሥጢር አለቀለት!” ብሎ ነበር። ይሁን እንጂ ይህ ፈጽሞ ከእውነት የራቀ አባባል ነበር። ሁለቱ ምሥክሮች እንደሞቱ አልቀሩም። እንዲህ እናነባለን:- “ከሦስቱ ቀን ተኩልም በኋላ ከእግዚአብሔር የወጣ የሕይወት መንፈስ ገባባቸው በእግሮቻቸውም ቆሙ፣ ታላቅም ፍርሃት በሚመለከቱት ላይ ወደቀባቸው። በሰማይም:- ወደዚህ ውጡ የሚላቸውን ታላቅ ድምፅ ሰሙ፤ ጠላቶቻቸውም እየተመለከቱአቸው ወደ ሰማይ በደመና ወጡ።” (ራእይ 11:11, 12) ስለዚህ ሕዝቅኤል በራእይ ተመልክቶት በነበረው ሸለቆ ውስጥ የነበሩት አጽሞች ያጋጠማቸውን የመሰለ ሁኔታ አጋጠማቸው። በእነዚህ ደረቅ አጽሞች ላይ ይሖዋ እፍ አለባቸውና ሕያው ሆኑ። ይህም የሆነው የእስራኤል ብሔር በባቢሎን ለ70 ዓመት በግዞት ከቆየ በኋላ እንደገና የሚወለድ መሆኑን ለማመልከት ነበር። (ሕዝቅኤል 37:1-14) እነዚህ የሕዝቅኤልና የራእይ ሁለት ትንቢቶች ዘመናዊ ፍጻሜያቸውን ያገኙት ይሖዋ ‘ሞተው’ የነበሩትን ምሥክሮቹን አዲስ ሕይወትና ኃይል ሰጥቶ ባስነሳበት በ1919 ነበር።
24. ሁለቱ ምሥክሮች ሕያዋን በሆኑ ጊዜ ሃይማኖታዊ አሳዳጆቻቸው ምን ተሰማቸው?
24 አሳዳጆቹን ምን ያህል የሚያስደነግጥ ነገር ነበር! የሁለቱ ምሥክሮች አጥንቶች በድንገት ሕያው ሆነው መንቀሳቀስ ጀመሩ። ለቀሳውስቱ ሊዋጥ የማይችል መራራ ኪኒን ሆኖባቸው ነበር። በእነርሱ ሴራ ምክንያት ታስረው የነበሩት አገልጋዮች ከእስር መውጣታቸውና ከቀረበባቸው ክስ ሙሉ በሙሉ ነፃ መደረጋቸው ይበልጡኑ መራራ ሆነባቸው። በተጨማሪም በ1919 የመስከረም ወር የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች በሴዳር ፖይንት፣ ኦሃዮ፣ ዩ ኤስ ኤ ከፍተኛ ስብሰባ ባደረጉ ጊዜ ትልቅ ድንጋጤ ወደቀባቸው። ትንሽ ቀደም ብሎ ከእሥራት የተፈታው ወንድም ጄ ኤፍ ራዘርፎርድ በዚህ ስብሰባ ላይ “መንግሥቱን ማስታወቅ” በተባለው ንግግሩ ተሰብሳቢዎቹን ለሥራ አነሳስቶአቸዋል። ይህ ንግግር በራእይ 15:2 እና በኢሳይያስ 52:7 ላይ የተመሠረተ ነበር። የዮሐንስ ክፍል አባሎች እንደገና ትንቢት መናገር ወይም በይፋ ለሕዝብ መስበክ ጀመሩ። በድፍረት የሕዝበ ክርስትናን ግብዝነት እያጋለጡ በብርታት ላይ ብርታት ጨመሩ።
-
-
ሁለቱን ምሥክሮች እንደገና ሕያው ማድረግራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
c በዚህ ጊዜ የአምላክ ሕዝቦች ያጋጠማቸውን ተሞክሮ በምንመረምርበት ጊዜ 42ቱ ወራት ቃል በቃል የሦስት ዓመት ተኩል ጊዜ የሚያመለክቱ እንደሆኑ ብንገነዘብም ሦስት ቀን ተኩሉ ግን ቃል በቃል የ84 ሰዓት ጊዜ አያመለክትም። የሦስት ቀን ተኩል ጊዜ ሁለት ጊዜ የተጠቀሰው (ቁጥር 9 እና 11 ላይ) ከዚያ በፊት ከነበረው የሦስት ዓመት ጊዜ ጋር ሲወዳደር አጭር ጊዜ እንደሚሆን ለማመልከት ይመስላል።
-