-
አምላክ የሚሰጠውን ማስጠንቀቂያ ሰምተህ እርምጃ ት ወ ስ ዳ ለ ህ ን ?መጠበቂያ ግንብ—1993 | መጋቢት 1
-
-
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ደግሞ ለጭንቀት ምክንያት ስለሆነ ሌላ ነገር ብዙ መነገር ተጀምሮአል። እርሱም የሰው ልጅ በአካባቢው ላይ እየፈጸመ ያለው ጥፋት ነው። ኢየሱስ ይህንን ሁኔታ በትንቢቱ ውስጥ በቀጥታ ባይጠቅሰውም መጪው ጥፋት ከመጀመሩ በፊት የሰው ልጅ ‘ምድርን ማጥፋት’ እንደሚጀምር ራእይ 11:18 ያመለክታል። የሰው ልጅ ምድርን በማበላሸት ላይ እንደሚገኝ የሚያመለክቱ ማስረጃዎች እጅግ ብዙ ናቸው። ኖርማን ማየርስ የተባሉት የአካባቢ ሁኔታ አማካሪ የዓለም ሁኔታ በ1988 በተባለው መጽሐፍ ላይ እንደጠቀሱት የሚከተለውን አስፈሪ መልእክት አስተላልፈዋል:- “በራሱ የሕይወት ዘመን የጅምላ እልቂት የመድረስ አደጋ የተደቀነበት ትውልድ ከዚህ በፊት ኖሮ አያውቅም። ወደፊትም ቢሆን ይህን የመሰለ ተፈታታኝ ሁኔታ የሚያጋጥመው ትውልድ አይኖርም። የአሁኑ ትውልድ ይህን ችግር ተገንዝቦ አንድ ነገር ማድረግ ካልቻለ ሊስተካከል የማይችል ጉዳት ስለሚደርስ ‘ሌላ ሙከራ’ ለማድረግ የሚያስችል ዕድል አይኖርም።”
በየካቲት 17, 1992 ኒውስዊክ መጽሔት ላይ በከባቢ አየር ውስጥ ስለሚገኘው የኦዞን ግርዶሽ መሳሳት የቀረበውን ረፖርት ተመልከት። ግሪንፒስ በተባለው የአካባቢ ሁኔታ የሚከታተል ድርጅት ውስጥ የሚሠሩት የኦዞን ስፔሺያሊስት አሌክዛንድራ አለን በአሁኑ ጊዜ የኦዞን መሳሳት “በምድር ላይ የሚኖረውን ሕይወት በሙሉ አደጋ ላይ በሚጥል ደረጃ ላይ ደርሶአል” እንዳሉ ተጠቅሶአል። — የምድር አካባቢ እየተበላሸ ስለመሄዱ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት በዚህ ገጽ ላይ የሚገኘውን ሳጥን ተመልከት።
-
-
አምላክ የሚሰጠውን ማስጠንቀቂያ ሰምተህ እርምጃ ት ወ ስ ዳ ለ ህ ን ?መጠበቂያ ግንብ—1993 | መጋቢት 1
-
-
[በገጽ 6 ላይ የሚገኝ ሣጥን]
አምላክ የሚሰጠውን ማስጠንቀቂያ ሰምተህ እርምጃ የጊዜው ምልክት የሆኑት የመኖሪያ አካባቢ ችግሮች
◻ ሕዝብ ጥቅጥቅ ብሎ በሚኖርባቸው የሰሜን ንፍቀ ክበብ አገሮች ያለው የኦዞን ግርዶሽ የሳይንስ ሊቃውንት ከጥቂት ዓመታት በፊት ያስቡት ከነበረው በእጥፍ በሚበልጥ መጠን እየሳሳ ሄዶአል።
◻ በየቀኑ በትንሹ 140 የሚያክሉ የእፅዋትና የእንስሳት ዝርያዎች ከምድር ገጽ በመጥፋት ላይ ናቸው።
◻ በከባቢ አየር ውስጥ የሚገኘው ሙቀት ወደ ጠፈር እንዳይሄድ አፍኖ የሚይዘው የካርቦን ዳይኦክሳይድ መጠን ከኢንዱስትሪ ዘመን በፊት ከነበረው መጠን በ26 በመቶ ጨምሮአል። ጭማሪው አሁንም አልተገታም።
◻ የምድርን ሙቀት መመዝገብ ከተጀመረበት ከ19ኛው መቶ ዘመን አጋማሽ ጀምሮ እንደ 1990 በጣም ሞቃት የሆነችበት ዘመን የለም። የምድር ሙቀት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከደረሰባቸው ሰባት ዓመታት መካከል ስድስቱ ከ1980 ወዲህ ያሉ ናቸው።
◻ የምድር ደኖች በየዓመቱ 17 ሚልዮን ሄክታር በሚያክል መጠን ይወድማሉ። ይህም የፊንላንድን ግማሽ የሚያክል ስፋት ያለው ቦታ ነው።
◻ የዓለም ሕዝብ ብዛት በየዓመቱ 92 ሚልዮን በሚያክል ብዛት ይጨምራል። ይህም በየዓመቱ የሜክሲኮን ሕዝቦች የሚያክሉ ሰዎች ይጨመራሉ ማለት ነው። ከእነዚህ መካከል 88 ሚልዮን የሚያክሉት የሚጨመሩት በመልማት ላይ በሚገኙ አገሮች ነው።
◻ 1.2 ቢልዮን የሚያክሉ ሰዎች ንጹሕ የመጠጥ ውኃ አያገኙም።
ዎርልድ ዎች የተባለ ድርጅት ባወጣው የዓለም ሁኔታ በ1992 በተባለው መጽሐፍ ገጽ 3, 4 መሠረት። ደብልዩ ደብልዩ ኖርተን እና ኩባንያው ኒውዮርክ፣ ለንደን
-