-
የአምላክ መንግሥት ተወለደ!ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
11. ዮሐንስ የሴቲቱን ልጅ መወለድ የገለጸው እንዴት ነው? ልጁስ “ልጅ፣ ወንድ ልጅ” የተባለው ለምንድን ነው?
11 አሕዛብ አምላክ ጣልቃ ሳይገባባቸው እንዲገዙ የተፈቀደላቸው ጊዜ በ1914 ተፈጸመ። (ሉቃስ 21:24) ሴቲቱም በዚህ በተወሰነው ጊዜ ልጅዋን ወለደች። “አሕዛብንም ሁሉ በብረት በትር ይገዛቸው ዘንድ ያለውን ልጅ ወንድ ልጅ ወለደች፤ ልጅዋም ወደ እግዚአብሔርና ወደ ዙፋኑ ተነጠቀ። ሴቲቱም ሺህ ከሁለት መቶ ስድሳ ቀን በዚያ እንዲመግቡአት በእግዚአብሔር ተዘጋጅቶላት ወደ ነበረው ስፍራ ወደ በረሀ ሸሸች።” (ራእይ 12:5, 6) ሕጻኑ “ልጅ፣ ወንድ ልጅ” ነበር። ዮሐንስ በዚህ ድርብ ስም የተጠቀመው ለምንድን ነው? አሕዛብን ለመግዛት ሙሉ ብቃት፣ ችሎታና ኃይል ያለው መሆኑን ለማመልከት ነው። በተጨማሪም የሕጻኑ መወለድ በጣም አስደሳችና ታላቅ ክንውን መሆኑን ያጎላል። የአምላክን ቅዱስ ምሥጢር በመፈጸም ረገድ ዋነኛ ድርሻ የሚያበረክት ድርጊት ነው። እንዲያውም ይህ ወንድ ልጅ “አሕዛብን ሁሉ በብረት በትር” የሚገዛቸው ነው!
-
-
የአምላክ መንግሥት ተወለደ!ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
13. ወንዱ ልጅ ‘ወደ አምላክና ወደ ዙፋኑ መወሰዱ’ ምን ያመለክታል?
13 ይሖዋ ሚስቱን ወይም አዲስ የተወለደውን ልጁን ሰይጣን እንዲውጥበት ፈጽሞ አይፈቅድም። ወንዱ ልጅ ሲወለድ “ወደ እግዚአብሔርና ወደ ዙፋኑ” ተነጥቆአል። ይህ በመደረጉም ይሖዋ ቅዱስ ስሙን ለማስቀደስ በመሣሪያነት የሚጠቀምበት የዚህ አዲስ የተወለደ መንግሥት ጠባቂና ተንከባካቢ ሆኖአል። ሴቲቱም በዚሁ ጊዜ አምላክ በምድረ በዳ ወዳዘጋጀላት ሥፍራ ሸሽታለች። ይህን በተመለከተ በኋላ ተጨማሪ ማብራሪያ ይሰጣል። በተጨማሪም ሰይጣን በሰማይ በተወለደው መንግሥት ላይ ጉዳት ሊያደርስ ፈጽሞ የማይችልበትን ሁኔታ የሚፈጥር ታላቅ ክንውን የሚፈጸምበት መድረክ ተመቻቸ። ታዲያ ይህ ክንውን ምንድን ነው?
-