-
የአምላክ መንግሥት ተወለደ!ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
17, 18. (ሀ) ሰይጣን ከሰማይ በመጣሉ በሰማይ እንዴት ያለ ስሜት እንደተፈጠረ ዮሐንስ ገልጾአል? (ለ) ዮሐንስ የሰማው ታላቅ ድምፅ ከየት የመነጨ ነበር?
17 በሰይጣን ላይ ይህን የመሰለ ታላቅ ውድቀት በደረሰበት ጊዜ በሰማይ እንዴት ያለ ደስታ እንደተፈጠረ ዮሐንስ ይነግረናል:- “ታላቅም ድምፅ በሰማይ ሰማሁ እንዲህ ሲል:- አሁን የአምላካችን ማዳንና ኃይል መንግሥትም የክርስቶስም ሥልጣን ሆነ፣ ቀንና ሌሊትም በአምላካችን ፊት የሚከሳቸው የወንድሞቻችን ከሳሽ ተጥሎአልና። እነርሱም ከበጉ ደም የተነሣ ከምስክራቸውም ቃል የተነሣ ድል ነሡት፣ ነፍሳቸውንም እስከ ሞት ድረስ አልወደዱም። ስለዚህ፣ ሰማይና በውስጡ የምታድሩ ሆይ፣ ደስ ይበላችሁ!”—ራእይ 12:10-12ሀ
-
-
የአምላክ መንግሥት ተወለደ!ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
20. ታማኝ ክርስቲያኖች ሰይጣንን ድል የነሱት እንዴት ነው?
20 “ከበጉ ደም የተነሳ” ጻድቅ ሆነው የተቆጠሩት ቅቡዓን ክርስቲያኖች ምንም ያህል ስደት ቢደርስባቸው ለአምላክና ለኢየሱስ ክርስቶስ መመስከራቸውን ቀጥለዋል። ይህ የዮሐንስ ክፍል ከ120 ዓመታት ለሚበልጥ ጊዜ የአሕዛብ ዘመን በ1914 ከመፈጸሙ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ታላላቅ ጉዳዮች ሲያመለክት ቆይቶአል። (ሉቃስ 21:24) በአሁኑ ጊዜ ደግሞ እጅግ ብዙ ሰዎች ከጎናቸው ተሰልፈው በታማኝነት በማገልገል ላይ ናቸው። ከእነዚህ ሰዎች መካከል አንዳቸውም ቢሆኑ “ሥጋን መግደል የሚቻላቸውን፣ ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን” አይፈሩም። ይህም በዘመናችን በይሖዋ ምሥክሮች ላይ በደረሱት ተሞክሮዎች ተደጋግሞ ተረጋግጦአል። በአፋቸው በሚናገሩት ቃልም ሆነ በጥሩ ክርስቲያናዊ ምግባራቸው ሰይጣን ሐሰተኛ መሆኑን ደጋግመው ስላረጋገጡ ድል ነስተውታል። (ማቴዎስ 10:28፤ ምሳሌ 27:11፤ ራእይ 7:9) ቅቡዓን ክርስቲያኖች ከሙታን ተነስተው ወደ ሰማይ ሲወሰዱ ወንድሞቻቸውን የሚከስሰው ሰይጣን በሰማይ ስለማይኖር በጣም ይደሰታሉ። የመላእክት ሠራዊት በሙሉ “በሰማይና በውስጡ የምታድሩ ሆይ! ደስ ይበላችሁ” የሚለውን ጥሪ ተቀብለው በደስታ የሚፈነድቁበት ጊዜ ነው።
-