የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • የአምላክ መንግሥት ተወለደ!
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • 17, 18. (ሀ) ሰይጣን ከሰማይ በመጣሉ በሰማይ እንዴት ያለ ስሜት እንደተፈጠረ ዮሐንስ ገልጾአል? (ለ) ዮሐንስ የሰማው ታላቅ ድምፅ ከየት የመነጨ ነበር?

      17 በሰይጣን ላይ ይህን የመሰለ ታላቅ ውድቀት በደረሰበት ጊዜ በሰማይ እንዴት ያለ ደስታ እንደተፈጠረ ዮሐንስ ይነግረናል:- “ታላቅም ድምፅ በሰማይ ሰማሁ እንዲህ ሲል:- አሁን የአምላካችን ማዳንና ኃይል መንግሥትም የክርስቶስም ሥልጣን ሆነ፣ ቀንና ሌሊትም በአምላካችን ፊት የሚከሳቸው የወንድሞቻችን ከሳሽ ተጥሎአልና። እነርሱም ከበጉ ደም የተነሣ ከምስክራቸውም ቃል የተነሣ ድል ነሡት፣ ነፍሳቸውንም እስከ ሞት ድረስ አልወደዱም። ስለዚህ፣ ሰማይና በውስጡ የምታድሩ ሆይ፣ ደስ ይበላችሁ!”—ራእይ 12:10-12ሀ

  • የአምላክ መንግሥት ተወለደ!
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • 20. ታማኝ ክርስቲያኖች ሰይጣንን ድል የነሱት እንዴት ነው?

      20 “ከበጉ ደም የተነሳ” ጻድቅ ሆነው የተቆጠሩት ቅቡዓን ክርስቲያኖች ምንም ያህል ስደት ቢደርስባቸው ለአምላክና ለኢየሱስ ክርስቶስ መመስከራቸውን ቀጥለዋል። ይህ የዮሐንስ ክፍል ከ120 ዓመታት ለሚበልጥ ጊዜ የአሕዛብ ዘመን በ1914 ከመፈጸሙ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ታላላቅ ጉዳዮች ሲያመለክት ቆይቶአል። (ሉቃስ 21:24) በአሁኑ ጊዜ ደግሞ እጅግ ብዙ ሰዎች ከጎናቸው ተሰልፈው በታማኝነት በማገልገል ላይ ናቸው። ከእነዚህ ሰዎች መካከል አንዳቸውም ቢሆኑ “ሥጋን መግደል የሚቻላቸውን፣ ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን” አይፈሩም። ይህም በዘመናችን በይሖዋ ምሥክሮች ላይ በደረሱት ተሞክሮዎች ተደጋግሞ ተረጋግጦአል። በአፋቸው በሚናገሩት ቃልም ሆነ በጥሩ ክርስቲያናዊ ምግባራቸው ሰይጣን ሐሰተኛ መሆኑን ደጋግመው ስላረጋገጡ ድል ነስተውታል። (ማቴዎስ 10:28፤ ምሳሌ 27:11፤ ራእይ 7:9) ቅቡዓን ክርስቲያኖች ከሙታን ተነስተው ወደ ሰማይ ሲወሰዱ ወንድሞቻቸውን የሚከስሰው ሰይጣን በሰማይ ስለማይኖር በጣም ይደሰታሉ። የመላእክት ሠራዊት በሙሉ “በሰማይና በውስጡ የምታድሩ ሆይ! ደስ ይበላችሁ” የሚለውን ጥሪ ተቀብለው በደስታ የሚፈነድቁበት ጊዜ ነው።

      ተፎካካሪ ወዮታ!

      21. ሰይጣን በምድርና በባሕር ላይ ወዮታ ያመጣው እንዴት ነው?

      21 ሰይጣን በሦስተኛው ወዮታ ምክንያት ሲንገላታ ስለቆየ አሁን የራሱን የረቀቀ ወዮታ በሰው ልጆች ላይ ለማውረድ ተነሳ። “ለምድርና ለባሕር ወዮላቸው፣ ዲያብሎስ ጥቂት ዘመን እንዳለው አውቆ በታላቅ ቁጣ ወደ እናንተ ወርዶአልና።” (ራእይ 12:12ለ) ሰይጣን ከሰማይ መጣሉና መባረሩ በሰይጣን ቁጥጥር ስር የሚኖሩ ራስ ወዳድ የሰው ልጆች ለሚያበላሹአት ግዑዝ ምድር ወዮታ ሆኖአል። (ዘዳግም 32:5) ከዚህ ይበልጥ ግን ሰይጣን የሚመራበት ‘ግዛ ወይም አጥፋ’ የሚለው መርሆ የሰብዓዊው ኅብረተሰብ አውታር በሆነው ምሳሌያዊ ምድርና ተነዋዋጭ የሆነውን ሕዝብ በሚያመለክተው ባሕር ላይ ወዮታ አምጥቶአል። የሰይጣን ቁጣ በሁለቱ የዓለም ጦርነቶች ጊዜ በሰይጣን ቁጥጥር ስር የሚኖሩት ብሔራት እርስ በርሳቸው ባስነሱት ቁጣ ተንፀባርቆአል። እስከዚህም ጊዜ ድረስ ይህ አጋንንታዊ የቁጣ ፍንዳታ መታየቱ አልቀረም። ይሁን እንጂ በዚህ ሁኔታ ለብዙ ጊዜ አይቀጥልም! (ማርቆስ 13:7, 8) የዲያብሎስ ዘዴዎች ክፉ ሊሆኑ ቢችሉም ሦስተኛው ወዮታ ማለትም የአምላክ መንግሥት የሚወስደው እርምጃ በሚታየው የሰይጣን ድርጅት ላይ የሚያስከትለውን ውጤት ያህል ሊሆኑ አይችሉም!

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ