-
በራእይ ምዕራፍ 13 ላይ የተገለጸው ሰባት ራሶች ያሉት አውሬ ምን ያመለክታል?የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
-
-
በራእይ ምዕራፍ 13 ላይ የተገለጸው ሰባት ራሶች ያሉት አውሬ ምን ያመለክታል?
መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?
በራእይ 13:1 ላይ የተገለጸው ሰባት ራሶች ያሉት አውሬ በዓለም ላይ ያለውን የፖለቲካ ሥርዓት በሙሉ ያመለክታል።
-
-
በራእይ ምዕራፍ 13 ላይ የተገለጸው ሰባት ራሶች ያሉት አውሬ ምን ያመለክታል?የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
-
-
አውሬው የወጣው “ከባሕር” ነው፤ ባሕሩ የሚያመለክተው ዓመፀኛ የሆነውን አብዛኛውን የሰው ዘር ሲሆን ሁሉም መንግሥታት የሚነሱት ከዚህ የሰው ዘር ማኅበረሰብ ነው።—ራእይ 13:1፤ ኢሳይያስ 17:12, 13
-
-
በራእይ ምዕራፍ 13 ላይ የተገለጸው ሰባት ራሶች ያሉት አውሬ ምን ያመለክታል?የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
-
-
“አሥር ቀንዶችና ሰባት ራሶች”
በራእይ ምዕራፍ 13 ላይ የተገለጸው አውሬ “አሥር ቀንዶችና ሰባት ራሶች” ምን እንደሚያመለክቱ በትክክል ለማወቅ በራእይ መጽሐፍ ውስጥ በሌላ ቦታ ላይ የተገለጸውን ‘የአውሬውን ምስል’ ማንነት ማወቃችን አስፈላጊ ነው፤ የአውሬው ምስል፣ ሰባት ራሶችና አሥር ቀንዶች እንዳሉት የተገለጸ ሲሆን ቀለሙም ደማቅ ቀይ ነው። (ራእይ 13:1, 14, 15፤ 17:3) መጽሐፍ ቅዱስ፣ የዚህ ቀይ አውሬ ሰባት ራሶች “ሰባት ነገሥታት” ወይም መንግሥታት እንደሆኑ ይገልጻል።—ራእይ 17:9, 10
በተመሳሳይም በራእይ 13:1 ላይ የተገለጸው አውሬ ሰባት ራሶች ሰባት መንግሥታትን ይወክላሉ፤ እነዚህ መንግሥታት በታሪክ ገናና የነበሩና በአምላክ ሕዝብ ላይ ጭቆና ያደረሱ የዓለም ኃያል የፖለቲካ ኃይሎችን ያመለክታሉ፤ እነሱም ግብፅ፣ አሦር፣ ባቢሎን፣ ሜዶ ፋርስ፣ ግሪክ፣ ሮምና አንግሎ አሜሪካ ናቸው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሱ አንዳንድ ቁጥሮች ምሳሌያዊ ትርጉም አላቸው። ለምሳሌ፣ አሥር ሙላትን በሌላ አባባል አንድን ነገር ሙሉ በሙሉ ይወክላል። በመሆኑም አሥሩ ቀንዶች፣ ትናንሽና ትላልቅ ሉዓላዊ መንግሥታትን በሙሉ ያመለክታሉ ብለን መደምደም እንችላለን፤ በእያንዳንዱ ቀንድ ላይ ዘውድ መኖሩ ደግሞ እነዚህ ሉዓላዊ መንግሥታት የራሳቸው ሥልጣን እንዳላቸውና በወቅቱ በሥልጣን ላይ ካለው የዓለም ኃያል መንግሥት ጋር ተመሳሳይ በሆነ ጊዜ ላይ እንደሚገዙ እንደሆኑ ያመለክታል።
-
-
የ666 ትርጉም ምንድን ነው?የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
-
-
የመጽሐፍ ቅዱስ የመጨረሻ መጽሐፍ እንደሚጠቁመው ይህ ቁጥር፣ ከባሕር የወጣው እንዲሁም አሥር ቀንዶችና ሰባት ራሶች ያሉት አውሬ ቁጥር ወይም ስም ነው። (ራእይ 13:1, 17, 18) አውሬው “በነገድ፣ በሕዝብ፣ በቋንቋና በብሔር ሁሉ ላይ” ሥልጣን የተሰጠውን በዓለም ላይ ያለውን አጠቃላይ የፖለቲካ ሥርዓት የሚወክል ነው። (ራእይ 13:7) አውሬው 666 የተባለ ቁጥር የተሰጠው መሆኑ ደግሞ አውሬውን የሚወክለው የፖለቲካ ሥርዓት በአምላክ ዓይን ሲታይ በከፍተኛ ሁኔታ እንከን ያለበት መሆኑን ያመለክታል። እንዲህ የምንለው ለምንድን ነው?
-