የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ስመ ጥፉ በሆነችው አመንዝራ ላይ መፍረድ
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • 13. መልአኩ ዮሐንስን በመንፈስ ወደ ምድረ በዳ በወሰደው ጊዜ ምን አስደናቂ ነገር ተመለከተ?

      13 ትንቢቱ ስለ ታላቂቱ አመንዝራና ስለሚደርስባት ዕጣ ምን የሚገልጸው ተጨማሪ ነገር አለ? ዮሐንስ የሚቀጥለውን ሲናገር በጣም አስደናቂ የሆነ ትዕይንት ልናይ ነው:- “በመንፈስም ወደ በረሐ [መልአኩ] ወሰደኝ የስድብም ስሞች በሞሉበት፣ ሰባት ራሶችና አሥር ቀንዶችም ባሉበት በቀይ አውሬ ላይ አንዲት ሴት ተቀምጣ አየሁ።”—ራእይ 17:3

  • ስመ ጥፉ በሆነችው አመንዝራ ላይ መፍረድ
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • 15. በ⁠ራእይ 13:1 ላይና በ⁠ራእይ 17:3 ላይ የተገለጹት አራዊት ምን ልዩነት አላቸው?

      15 ይህም አውሬ ሰባት ራሶችና አሥር ቀንዶች ነበሩት። ታዲያ ይህ አውሬ ዮሐንስ ቀደም ሲል ከተመለከተው ባለ ሰባት ራስና ባለ አሥር ቀንድ አውሬ ጋር አንድ ነውን? (ራእይ 13:1) አይደለም፣ ልዩነት አላቸው። ይኸኛው አውሬ መልኩ ቀይ ሲሆን እንደ ፊተኛው አውሬ በራሶቹ ላይ ዘውዶች የሉትም። የስድብ ስም የተሸከመው በራሶቹ ላይ ብቻ ሳይሆን “የስድብ ስሞች የሞሉበት” ነው። ሆኖም ግን በዚህ አዲስ አውሬና ቀደም ባለው አውሬ መካከል አንድ ዓይነት ዝምድና መኖር አለበት። በብዙ ሁኔታዎች መመሳሰላቸው እንዲሁ በአጋጣሚ የሆነ አይደለም።

      16. ቀዩ አውሬ ማን ነው? ዓላማውስ ምን እንደሆነ ተገልጾአል?

      16 ታዲያ ይህ አውሬ ምንድን ነው? በግ የሚመስለው ባለ ሁለት ቀንድ አውሬ ማለትም የአንግሎ አሜሪካ ጥምር ኃይል እንዲቋቋም ያደረገው የአውሬው ምስል መሆን ይኖርበታል። የአውሬው ምስል ከተሠራ በኋላ ባለ ሁለት ቀንዱ አውሬ ለአውሬው ምስል ትንፋሽ እንዲሰጠው ተፈቅዶለታል። (ራእይ 13:14, 15) አሁን ዮሐንስ የተመለከተው ሕያው ሆኖ የሚተነፍሰውን ምስል ነው። ይህ አውሬ ባለ ሁለት ቀንዱ አውሬ በ1920 ወደ ሕይወት ያመጣውን የመንግሥታት ቃል ኪዳን ማኅበርን ያመለክታል። የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት የነበሩት ዊልሰን ማኅበሩ “ለሰዎች ሁሉ ሰላም የሚዳረስበትና የጦርነት ስጋት ለዘላለም ተጠርጎ የሚጠፋበት መድረክ እንደሚሆን” ተናግረው ነበር። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ተብሎ ትንሣኤ ባገኘ ጊዜ በተቋቋመበት ቻርተር መሠረት የማኅበሩ ዓላማ “ዓለም አቀፍ ሰላምና ደኅንነት ማስጠበቅ” ነበር።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ