-
“ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች!”ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
27. (ሀ) ማጭድ የያዘው መልአክ የምድሩን የወይን ዘለላ ማጨድ ሲጀምር ምን ይሆናል? (ለ) የአጨዳው ስፋት ምን ያህል እንደሚሆን የሚያመለክቱ የዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎች ትንቢቶች የትኞቹ ናቸው?
27 የቅጣቱ ፍርድ መፈጸም ይኖርበታል! “መልአኩም ማጭዱን ወደ ምድር ጣለው፣ በምድርም ካለው ከወይን ዛፍ ቆርጦ ወደ ታላቁ ወደ እግዚአብሔር ቁጣ መጥመቂያ ጣለ። የወይኑም መጥመቂያ ከከተማ ውጭ ተረገጠ፣ እስከ ፈረሶች ልጓምም የሚደርስ ደም ርቀቱ ሺህ ስድስት መቶ ምዕራፍ ሆኖ ከመጥመቂያው ወጣ።” (ራእይ 14:19, 20) ይሖዋ በዚህ የወይን ዘለላ ላይ መቆጣቱን ቀደም ሲል አስታውቆአል። (ሶፎንያስ 3:8) በኢሳይያስ መጽሐፍ ውስጥ የተነገረው ትንቢት የወይኑ መጥመቂያ በሚረገጥበት ጊዜ ጠቅላላ ብሔራት እንደሚጠፉ በማያሻማ ሁኔታ ገልጾአል። (ኢሳይያስ 63:3-6) ኢዩኤልም ብዙ “ሕዝቦች” “በፍርድ ሸለቆ” ውስጥ ባለው “መጥመቂያ” ተረግጠው እንደሚጠፉ ተናግሮአል። (ኢዩኤል 3:12-14) በእውነትም ተወዳዳሪ የማይገኝለት ታላቅ መከር ነው። በዮሐንስ ራእይ መሠረት የወይን ፍሬዎቹ ብቻ ሳይሆን መላው የወይን ዛፍ ተቆርጦ በወይኑ መጥመቂያ ውስጥ ይጣልና ይረገጣል። ስለዚህ የምድሩ የወይን ዛፍ ተረግጦ ይጠፋል። ዳግመኛም ሊያቆጠቁጥ አይችልም።
-
-
“ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች!”ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
30 በፍጻሜው ዘመን ውስጥ የምንኖር እንደመሆናቸን መጠን የእነዚህ ሁለት መከሮች ራእይ ለእኛ ትልቅ ትርጉም አለው። የሰይጣንን የወይን ዘለላ ፍሬዎች ለማየት ሩቅ መሄድ አያስፈልገንም። ጽንስ ማስወረድና ሌሎች የነፍስ ግድያ ተግባሮች፣ ግብረ ሰዶም፣ አጭበርባሪነትና የተፈጥሮ ፍቅር መጥፋት ይህንን ዓለም በይሖዋ ፊት በጣም አስጸያፊ አድርጎታል። የሰይጣን የወይን ዘለላ “የመርዛማ ተክል ፍሬና እሬት” አፍርቶአል። የአጥፊነት ባሕርዩና በጣዖት አምልኮ ላይ የተመሠረተው አኗኗሩ የሰው ልጆችን ታላቅ ፈጣሪ የሚያዋርድ ሆኖአል። (ዘዳግም 29:18፤ 32:5፤ ኢሳይያስ 42:5, 8) ለይሖዋ ውዳሴ ኢየሱስ በመሰብሰብ ላይ ባለው የጤናማ ፍሬዎች የመከር ሥራ ከዮሐንስ ክፍል ጋር ለመተባበር መቻል በጣም ትልቅ መብት ነው። (ሉቃስ 10:2) ሁላችንም በዚህ ዓለም የወይን ዘለላ ላለመበከል ቁርጥ ውሳኔ እናድርግ። የይሖዋ የቁጣ ፍርድ በሚፈጸምበት ጊዜ ከምድሪቱ የወይን ዘለላ ጋር አብረን እንዳንረገጥ እንጠንቀቅ።
-