የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • የአምላክ ቁጣ ወደ ፍጻሜ ደረሰ
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • 17. (ሀ) የአምስተኛው ጽዋ መፍሰስ የአውሬውን መንግሥት ከዋጠው መንፈሣዊ ጨለማ ጋር የሚዛመደው እንዴት ነው? (ለ) አምስተኛው የአምላክ ቁጣ ሲፈስስ ሰዎች ምን ተሰማቸው?

      17 የዚህ አውሬ መንግሥት ገና ከመጀመሪያው አንስቶ በመንፈሣዊ ጨለማ ውስጥ የሚገኝ ነው። (ከ⁠ማቴዎስ 8:12⁠ና ከ⁠ኤፌሶን 6:11, 12 ጋር አወዳድር።) አምስተኛው ጽዋ ይህን ጨለማ በተጠናከረ ሁኔታ የሚያጋልጥ ሕዝባዊ ማስታወቂያ ነበር። እንዲያውም ይህ የአምላክ የቁጣ ጽዋ በምሳሌያዊው አውሬ ዙፋን ላይ መፍሰሱ በትዕይንታዊ ሁኔታ ተገልጾአል። “መንግሥቱም ጨለማ ሆነች፣ ከሥቃይም የተነሣ መላሶቻቸውን ያኝኩ ነበር። ከሥቃያቸውና ከቁስላቸውም የተነሣ የሰማይን አምላክ ተሳደቡ፣ ከሥራቸውም ንስሐ አልገቡም።”—ራእይ 16:10ለ, 11

  • የአምላክ ቁጣ ወደ ፍጻሜ ደረሰ
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • 19. በ⁠ራእይ 16:10, 11 መሠረት ሰይጣን የዚህ ዓለም አምላክ እንደሆነ መጋለጡ ምን ውጤት አስከተለ?

      19 ሰይጣን የዓለም ገዥ በመሆኑ ብዙ ችግርና መከራ አምጥቶአል። ረሐብ፣ ጦርነት፣ ዓመፅ፣ ወንጀል፣ የዕፅ ሱሰኝነት፣ ዝሙት፣ በፆታ ግንኙነት የሚተላለፉ በሽታዎች፣ አጭበርባሪነት፣ ሃይማኖታዊ ግብዝነትና ሌሎች እነዚህን የመሰሉ ሁኔታዎች የሰይጣን ሥርዓት መለያ ባሕርያት ሆነዋል። (ከ⁠ገላትያ 5:19-21 ጋር አወዳድር።) ሰይጣን የዚህ ዓለም አምላክ እንደሆነ መጋለጡ የእርሱን የአቋም ደረጃ ተከትለው ለሚኖሩ ሰዎች እፍረትና ሥቃይ አስከትሎባቸዋል። በተለይ በሕዝበ ክርስትና ውስጥ ያሉ ሰዎች “ከሥቃይ የተነሳ መላሶቻቸውን ያኝኩ ነበር።” ብዙ ሰዎች እውነት አኗኗራቸውን ስለሚያጋልጥባቸው ይጠሉታል። አንዳንዶች ደግሞ የእውነት መልእክት ስለሚያስፈራቸው መልእክቱን የሚያስፋፉትን ሰዎች ያሳድዳሉ። የአምላክን መንግሥት አይቀበሉም፣ የይሖዋንም ቅዱስ ስም ይነቅፋሉ። ሃይማኖታዊ በሽተኞችና ቁስለኞች መሆናቸው ግልጽ ሆኖ ስለታየባቸው የሰማይን አምላክ ይሳደባሉ። ይሁን እንጂ “ከሥራቸው ንስሐ” አይገቡም። ስለዚህ ይህ ሥርዓት ከመፈጸሙ በፊት የዓለም ሕዝቦች በሙሉ ወደ ክርስትና ይለወጣሉ ብለን ልንጠባበቅ አንችልም።—ኢሳይያስ 32:6

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ