የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • በታላቂቱ ባቢሎን ላይ የሚፈጸም የሞት ቅጣት
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • 1. መልአኩ ቀዩን አውሬ የገለጸው እንዴት ነው? የራእይን ምልክቶች ለመረዳት የሚያስፈልገው ምን ዓይነት ጥበብ ነው?

      መልአኩ በ⁠ራእይ 17:3 ላይ ስለተጠቀሰው ቀይ አውሬ ተጨማሪ መግለጫ ሲሰጥ ለዮሐንስ እንዲህ አለው:- “ጥበብ ያለው አእምሮ በዚህ ነው። ሰባቱ ራሶች ሴቲቱ የተቀመጠችባቸው ሰባት ተራራዎች ናቸው ሰባት ነገሥታት ደግሞ ናቸው፤ አምስቱ ወድቀዋል አንዱም አለ፣ የቀረውም ገና አልመጣም፤ ሲመጣም፣ ጥቂት ጊዜ ሊቆይ ይገባዋል።” (ራእይ 17:9, 10) እዚህ ላይ መልአኩ ያሳወቀው በራእይ መጽሐፍ ውስጥ የተገለጹትን ምልክቶች ለማስተዋል የሚያስችለውን ከላይ የሚመጣ ጥበብ ነው። (ያዕቆብ 3:17) ይህ ጥበብ የዮሐንስ ክፍል አባሎችና ባልንጀሮቻቸው ይህ የምንኖርበት ጊዜ ምን ያህል አሳሳቢ ጊዜ መሆኑን እንዲያስተውሉ ያስችላቸዋል። ሙሉ በሙሉ ለይሖዋ የተወሰኑ ልቦች አሁን ሊፈጸም የተቃረበውን የይሖዋ ፍርድ እንዲገነዘቡ ያደርጋቸዋል። ለይሖዋም ጤናማ ፍርሐት እንዲያድርባቸው ያደርጋል። ምሳሌ 9:10 እንደሚለው “የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን [“ይሖዋን፣” NW] መፍራት ነው፣ ቅዱሱንም ማወቅ ማስተዋል ነው።” ታዲያ ይህ መለኮታዊ ጥበብ ስለ አውሬው ምን ነገር ይገልጥልናል?

      2. የቀዩ አውሬ ሰባት ራሶች ትርጉም ምንድን ነው? ‘አምስቱ የወደቁትና አንዱ የኖረው’ እንዴት ነው?

      2 የዚህ አስፈሪ አውሬ ሰባት ራሶች ሰባት “ተራሮችን” ወይም ሰባት “ነገሥታትን” ያመለክታሉ። ሁለቱም ቃሎች በቅዱሳን ጽሑፎች ውስጥ መንግሥታዊ ሥልጣናትን ለማመልከት ተሠርቶባቸዋል። (ኤርምያስ 51:24, 25፤ ዳንኤል 2:34, 35, 44, 45) በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በአምላክ ሕዝቦች ላይ ተጽዕኖ የነበራቸው ስድስት የዓለም ኃያል መንግሥታት እንደነበሩ ተገልጾአል። እነርሱም ግብጽ፣ አሦር፣ ባቢሎን፣ ሜዶ-ፋርስ፣ ግሪክና ሮም ናቸው። ከእነዚህ መካከል ዮሐንስ ራእዩን በተቀበለበት ጊዜ አምስቱ መጥተው ያለፉ ሲሆን ሮም ገና ከዓለም ኃያልነቱ አልወረደም ነበር። ይህም “አምስቱ ወድቀዋል፣ አንዱም አለ” ከሚለው ቃል ጋር ይስማማል። ይሁን እንጂ ገና የሚመጣው “የቀረው” መንግሥትስ?

  • በታላቂቱ ባቢሎን ላይ የሚፈጸም የሞት ቅጣት
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • 6. የትኞቹ አዳዲስ ግዛቶች ተቋቁመዋል? ከሁሉም በላይ የተሳካለት የትኛው ነበር?

      6 ከ15ኛው መቶ ዘመን ጀምሮ ግን አንዳንድ አገሮች ፈጽሞ አዳዲስ የሆኑ መንግሥታትን ማቋቋም ጀምረው ነበር። ከእነዚህ አዲስ ግዛት አስፋፊ ኃይላት አንዳንዶቹ ቀድሞ የሮማ ቅኝ ግዛት በነበሩ አካባቢዎች የሚገኙ ቢሆኑም ግዛታቸው የሮም ግዛት ቅጥያ አልነበረም። ፖርቱጋል፣ ስፓኝ፣ ፈረንሣይና ሆላንድ የሠፊ ግዛት ባለቤቶች ሆኑ። ከሁሉም በላይ የተሳካላት ግን ‘ፀሐይ አይጠልቅበትም’ የተባለ ሠፊ ግዛት ልትመሠርት የቻለችው የብሪታንያ መንግሥት ነበረች። የብሪታንያ ግዛት በሰሜን አሜሪካ፣ በአፍሪካ፣ በሕንድ፣ በደቡብ ምሥራቅ እስያና እስከ ፓስፊክ ውቅያኖስ ድረስ የተስፋፋ ነበረ።

      7. ጥምር የዓለም ኃያል መንግሥት የተቋቋመው እንዴት ነው? ሰባተኛው ራስ ወይም ሰባተኛው የዓለም ኃያል መንግሥት ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆይ ዮሐንስ ተናገረ?

      7 በ19ኛው መቶ ዘመን በሰሜን አሜሪካ ከሚገኙት ቅኝ ግዛቶች አንዳንዶቹ ከብሪታንያ ተገንጥለው ዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ የሚባል ነጻ መንግሥት መሠረቱ። በአዲሱ ብሔርና በቀድሞው እናት አገር መካከል የፖለቲካ ግጭት መኖሩ አልቀረም ነበር። ቢሆንም አንደኛው የዓለም ጦርነት ሁለቱም አገሮች የጋራ ጥቅም እንዳላቸው እንዲገነዘቡ ስላስገደዳቸው በመካከላቸው ልዩ የሆነ ዝምድና ተመሠረተ። በዚህም መንገድ በአሁኑ ጊዜ በዓለም ላይ በብልጽግናው ተወዳዳሪ በሌለው በዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካና በዓለም በስፋቱ አንደኛ የሆነ የንጉሠ ነገሥት ግዛት እምብርት በሆነችው በብሪታንያ የተቋቋመ ጥምር የዓለም ኃያል መንግሥት ተመሠረተ። ስለዚህ እስከ መጨረሻው ጊዜ የሚቆየውና የዘመናችን የይሖዋ ምሥክሮች ለመጀመሪያ ጊዜ የተቋቋሙበትን ክልል ጭምር የሚገዛው ሰባተኛው ራስ ወይም የዓለም ኃያል መንግሥት ይህ ነው። ሰባተኛው የዓለም ኃያል መንግሥት የሚቆየው የአምላክ መንግሥት ብሔራዊ ግዛቶችን ሁሉ እስከሚያጠፋበት ጊዜ ድረስ ብቻ ስለሆነ የግዛቱ ዘመን ከስድስተኛው ራስ ጋር ሲወዳደር “ጥቂት ጊዜ” ነው።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ