የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • በታላቂቱ ባቢሎን ላይ የሚፈጸም የሞት ቅጣት
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • 11. የይሖዋ መልአክ በምሳሌያዊው ቀይ አውሬ ላይ ስላሉት አሥር ቀንዶች ምን ተናግሮአል?

      11 በቀደመው የራእይ መጽሐፍ ምዕራፍ ላይ ስድስተኛውና ሰባተኛው መላእክት የአምላክን የቁጣ ጽዋ አፍስሰው ነበር። የምድር ነገሥታትም በአርማጌዶን ወደሚደረገው የአምላክ ጦርነት በመሰብሰብ ላይ እንደሆኑና ‘ታላቂቱ ባቢሎንም’ በአምላክ ፊት እንደምትታሰብ ተነግሮናል። (ራእይ 16:1, 14, 19) አሁን ደግሞ የአምላክ ፍርድ በእነዚህ ላይ እንዴት እንደሚፈጸም በተብራራ ሁኔታ እንማራለን። የይሖዋ መልአክ ዮሐንስን ሲያነጋግረው እናዳምጥ:- “ያየሃቸውም አሥሩ ቀንዶች ገና መንግሥትን ያልተቀበሉ አሥር ነገሥታት ናቸው፣ ዳሩ ግን ከአውሬው ጋር ለአንድ ሰዓት እንደ ነገሥታት ሥልጣንን ይቀበላሉ። እነዚህ አንድ አሳብ አላቸው፣ ኃይላቸውንና ሥልጣናቸውንም ለአውሬው ይሰጣሉ። እነዚህ በጉን ይወጋሉ፤ በጉም የጌቶች ጌታና የነገሥታት ንጉሥ ስለሆነ እነርሱን ድል ይነሣል፣ ከእርሱም ጋር ያሉ የተጠሩና የተመረጡ የታመኑም ደግሞ ድል ይነሣሉ።”—ራእይ 17:12-14

  • በታላቂቱ ባቢሎን ላይ የሚፈጸም የሞት ቅጣት
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • 13. አሥሩ ቀንዶች “አንድ አሳብ” የኖራቸው በምን መንገድ ነው? ይህስ በበጉ ላይ ምን ዓይነት ዝንባሌ እንዲኖር አድርጎአል?

      13 በዛሬው ጊዜ እነዚህን አሥር ቀንዶች ከሚያንቀሳቅሱት ጠንካራ ኃይሎች አንዱ ብሔራዊ ስሜት ነው። የአምላክን መንግሥት ከመቀበል ይልቅ ብሔራዊ ሉዓላዊነታቸውን ለማስጠበቅ ስለሚፈልጉ “አንድ አሳብ” አላቸው። የመንግሥታት ቃል ኪዳን ማኅበርና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባላት የሆኑትም ለዚህ ዓላማ ነው። የዓለምን ሰላም ለማስጠበቅና በዚያውም ሕልውናቸውን ለማስከበር ነው። ቀንዶቹ እንዲህ ያለ አቋምና ዝንባሌ ስላላቸው “የጌቶች ጌታና የነገሥታት ንጉሥ” የሆነውን በጉን እንደሚቃወሙ የታወቀ ነው። ምክንያቱም በኢየሱስ ክርስቶስ የሚመራው የአምላክ መንግሥት በቅርቡ እነዚህን መንግሥታት በሙሉ አጥፍቶ እርሱ ብቻውን በቦታቸው እንዲቆም የይሖዋ ዓላማ ነው።—ዳንኤል 7:13, 14፤ ማቴዎስ 24:30፤ 25:31-33, 46

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ