የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • በታላቂቱ ባቢሎን ላይ የሚፈጸም የሞት ቅጣት
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • 11. የይሖዋ መልአክ በምሳሌያዊው ቀይ አውሬ ላይ ስላሉት አሥር ቀንዶች ምን ተናግሮአል?

      11 በቀደመው የራእይ መጽሐፍ ምዕራፍ ላይ ስድስተኛውና ሰባተኛው መላእክት የአምላክን የቁጣ ጽዋ አፍስሰው ነበር። የምድር ነገሥታትም በአርማጌዶን ወደሚደረገው የአምላክ ጦርነት በመሰብሰብ ላይ እንደሆኑና ‘ታላቂቱ ባቢሎንም’ በአምላክ ፊት እንደምትታሰብ ተነግሮናል። (ራእይ 16:1, 14, 19) አሁን ደግሞ የአምላክ ፍርድ በእነዚህ ላይ እንዴት እንደሚፈጸም በተብራራ ሁኔታ እንማራለን። የይሖዋ መልአክ ዮሐንስን ሲያነጋግረው እናዳምጥ:- “ያየሃቸውም አሥሩ ቀንዶች ገና መንግሥትን ያልተቀበሉ አሥር ነገሥታት ናቸው፣ ዳሩ ግን ከአውሬው ጋር ለአንድ ሰዓት እንደ ነገሥታት ሥልጣንን ይቀበላሉ። እነዚህ አንድ አሳብ አላቸው፣ ኃይላቸውንና ሥልጣናቸውንም ለአውሬው ይሰጣሉ። እነዚህ በጉን ይወጋሉ፤ በጉም የጌቶች ጌታና የነገሥታት ንጉሥ ስለሆነ እነርሱን ድል ይነሣል፣ ከእርሱም ጋር ያሉ የተጠሩና የተመረጡ የታመኑም ደግሞ ድል ይነሣሉ።”—ራእይ 17:12-14

  • በታላቂቱ ባቢሎን ላይ የሚፈጸም የሞት ቅጣት
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • 13. አሥሩ ቀንዶች “አንድ አሳብ” የኖራቸው በምን መንገድ ነው? ይህስ በበጉ ላይ ምን ዓይነት ዝንባሌ እንዲኖር አድርጎአል?

      13 በዛሬው ጊዜ እነዚህን አሥር ቀንዶች ከሚያንቀሳቅሱት ጠንካራ ኃይሎች አንዱ ብሔራዊ ስሜት ነው። የአምላክን መንግሥት ከመቀበል ይልቅ ብሔራዊ ሉዓላዊነታቸውን ለማስጠበቅ ስለሚፈልጉ “አንድ አሳብ” አላቸው። የመንግሥታት ቃል ኪዳን ማኅበርና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባላት የሆኑትም ለዚህ ዓላማ ነው። የዓለምን ሰላም ለማስጠበቅና በዚያውም ሕልውናቸውን ለማስከበር ነው። ቀንዶቹ እንዲህ ያለ አቋምና ዝንባሌ ስላላቸው “የጌቶች ጌታና የነገሥታት ንጉሥ” የሆነውን በጉን እንደሚቃወሙ የታወቀ ነው። ምክንያቱም በኢየሱስ ክርስቶስ የሚመራው የአምላክ መንግሥት በቅርቡ እነዚህን መንግሥታት በሙሉ አጥፍቶ እርሱ ብቻውን በቦታቸው እንዲቆም የይሖዋ ዓላማ ነው።—ዳንኤል 7:13, 14፤ ማቴዎስ 24:30፤ 25:31-33, 46

      14. የዓለም ገዥዎች ከበጉ ጋር ሊዋጉ የሚችሉት እንዴት ነው? ውጤቱስ ምን ይሆናል?

      14 እርግጥ፣ የዚህ ዓለም ገዥዎች በኢየሱስ ላይ ምንም ለማድረግ አይችሉም። እርሱ የሚኖረው እነርሱ ሊደርሱ በማይችሉበት በሰማይ ነው። ይሁን እንጂ ከሴቲቱ ዘር የቀሩት የኢየሱስ ወንድሞች አሁንም በምድር ላይ ናቸው። ለጥቃትም የተጋለጡ መስለው የሚታዩ ናቸው። (ራእይ 12:17) ከቀንዶቹ መካከል ብዙዎቹ እነዚህን ቀሪዎች አምርረው እንደሚጠሉ አሳይተዋል። ይህንንም በማድረጋቸው በጉን ወግተውታል። (ማቴዎስ 25:40, 45) ይሁን እንጂ ከጥቂት ጊዜ በኋላ የአምላክ መንግሥት ‘እነዚህን ሁሉ መንግሥታት የምትፈጭበትና የምታደቅበት’ ጊዜ ይመጣል። (ዳንኤል 2:44) በቅርቡ እንደምንመለከተው በዚያ ጊዜ የምድር ነገሥታት በሙሉ እስከ መጨረሻው ድረስ ከበጉ ጋር ይዋጋሉ። (ራእይ 19:11-21) ሆኖም ግን ብሔራት በዚህ ጥቃታቸው እንደማይሳካላቸው የሚያስገነዝብ በቂ መረጃ ተሰጥቶናል። እነዚህ ነገሥታትም ሆኑ ቀይ አውሬ የተባለው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት “አንድ አሳብ” ቢኖራቸውም ታላቁን “የጌቶች ጌታና የነገሥታት ንጉሥ” ሊያሸንፉ አይችሉም። ‘የተመረጡትንና ከእርሱ ጋር በታማኝነት የጸኑትን’ ገና በምድር ላይ የቀሩትን ቅቡዓንንም ቢሆን ሊያሸንፉ አይችሉም። እነዚህም ቢሆኑ በፍጹም አቋማቸው ጸንተው የሰይጣንን ክስ ሐሰተኛነት በማረጋገጥ ድል ይነሳሉ።—ሮሜ 8:37-39፤ ራእይ 12:10, 11

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ