የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ታላቂቱ ከተማ ድምጥማጥዋ ጠፋ
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • 23. ከሰማይ የተሰማው ድምፅ ከታላቂቱ ባቢሎን ሸሽቶ መውጣት በጣም አጣዳፊ መሆኑን አጠንክሮ የገለጸው እንዴት ነው?

      23 ከዓለማዊ ሃይማኖቶች አባልነት በመውጣትና ፈጽሞ በመለየት ከታላቂቱ ባቢሎን መሸሽ በእርግጥ አጣዳፊ ጉዳይ ነውን? ለዚህች አስቀያሚ አሮጊት፣ ለታላቂቱ ባቢሎን ከአምላክ ጋር የሚመሳሰል አመለካከት ሊኖረን ስለሚገባ በእርግጥም አጣዳፊ ነው። አምላክ ታላቂቱ ጋለሞታ ብሎ ለመጥራት ቅር አልተሰኘም። በዚህም ምክንያት ከሰማይ የመጣው ድምፅ ስለዚህች አመንዝራ ተጨማሪ መግለጫ ለዮሐንስ ሰጥቶታል። “ኃጢአትዋ እስከ ሰማይ ድረስ ደርሶአልና፣ እግዚአብሔርም ዓመፃዋን አሰበ። እርስዋ እንደ ሰጠች መጠን ብድራት መልሱላት፣ እንደ ሥራዋም ሁለት እጥፍ ደርቡባት በቀላቀለችው ጽዋ ሁለት እጥፍ አድርጋችሁ ቀላቅሉባት፤ ራስዋን እንደ አከበረችና እንደ ተቀማጠለች ልክ ሥቃይና ኃዘን ስጡአት። በልብዋ፣ ንግሥት ሆኜ እቀመጣለሁ ባልቴትም አልሆንም ኃዘንንም ከቶ አላይም ስላለች፣ ስለዚህ በአንድ ቀን ሞትና ኀዘን ራብም የሆኑ መቅሠፍቶችዋ ይመጣሉ፣ በእሳትም ትቃጠላለች፤ የሚፈርድባት እግዚአብሔር [“ይሖዋ፣” NW] ብርቱ ነውና።”—ራእይ 18:5-8

  • ታላቂቱ ከተማ ድምጥማጥዋ ጠፋ
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • 27. በጥንትዋ ባቢሎን ላይ የተፈጸመውና በታላቂቱ ባቢሎን ላይ የሚፈጸመው ፍርድ ተመሳሳይነት ያለው እንዴት ነው?

      27 የጥንትዋ ባቢሎን የወደቀችውና በመጨረሻም ባድማ የሆነቸው ለኃጢአትዋ መቀጫ እንዲሆናት ነበር። “ፍርድዋ እስከ ሰማይ ደርሶአልና።” (ኤርምያስ 51:9) በተመሳሳይም የታላቂቱ ባቢሎን ኃጢአት ይሖዋ እስኪያየው ድረስ ‘ወደ ሰማይ ደርሶአል።’ የፍትሕ አጉዳይነት፣ የጣዖት አምልኮ፣ የሥነ ምግባራዊ ብልግና፣ የጭቆናና የግድያ ወንጀል ተከምሮባታል። የጥንትዋ ባቢሎን የወደቀችው በከፊል በይሖዋ ቤተ መቅደስና በእውነተኛ አምላኪዎቹ ላይ ላደረሰችው ጉዳት በቀል እንዲሆን ነበር። (ኤርምያስ 50:8, 14፤ 51:11, 35, 36) በተመሳሳይም የታላቂቱ ባቢሎን ውድቀትና የመጨረሻ ጥፋት ባለፉት በርካታ መቶ ዘመናት በአምላክ እውነተኛ አምላኪዎች ላይ ለፈጸመችው በደል የበቀል መግለጫ ነው። በእርግጥም “አምላካችን የሚበቀልበት ቀን” የሚጀምረው በታላቂቱ ባቢሎን ጥፋት ነው።—ኢሳይያስ 34:8-10፤ 61:2፤ ኤርምያስ 50:28

      28. ይሖዋ በታላቂቱ ባቢሎን ላይ የሚፈጽመው የትኛውን የፍትሕ ማስፈጸሚያ ደረጃ ነው? ለምንስ?

      28 በሙሴ ሕግ መሠረት አንድ እሥራኤላዊ ከአገሩ ሰዎች የአንዱን ንብረት ቢሰርቅ እጅግ ቢያንስ የሰረቀውን ንብረት እጥፍ አድርጎ መመለስ ነበረበት። (ዘጸአት 22:1, 4, 7, 9) በመጪው የታላቂቱ ባቢሎን ጥፋት ጊዜም ይሖዋ ከዚህ ጋር የሚመሳሰል ፍርድ እንዲፈጸም ያደርጋል። እርስዋ ካደረገችው በእጥፍ የሚበልጥ እንድትቀበል ይደረጋል። ታላቂቱ ባቢሎን ለበደለቻቸው ሰዎች ምንም ዓይነት ምህረት ስላላሳየች ለእርሷም ምህረት አይደረግላትም። ‘በአሳፋሪ የቅምጥልነት ኑሮ’ ለመኖር ስትል የምድር ሕዝቦችን ስትቦጠቡጥ ኖራለች። አሁን ግን መከራና ሐዘን ይመጣባታል። የጥንትዋ ባቢሎን ምንም ነገር ሊነካት እንደማይችል ትተማመን ስለነበረ “መበለትም ሆኜ አልኖርም፣ የወላድ መካንነትም አላውቅም” እያለች ትታበይ ነበር። (ኢሳይያስ 47:8, 9, 11) ታላቂቱ ባቢሎንም ልክ እንደርስዋ ምንም ነገር ሊደርስባት እንደማይችል ተማምናለች። ይሁን እንጂ “ብርቱ” የሆነው ፈራጅዋ ይሖዋ የበየነባት ጥፋት “በአንድ ቀን” እንደሆነ ያህል ፈጥኖ ይመጣባታል።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ