-
ያህን ስለ ፍርዶቹ አወድሱት!ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
1. ዮሐንስ ‘በሰማይ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ሲናገር የሰማው’ ምንድን ነው?
ከዚያ በኋላ ታላቂቱ ባቢሎን አትኖርም! እንዲህ ያለው ዜና በጣም ያስደስታል። ዮሐንስም በሰማይ የደስታ ውዳሴ ድምፅ መስማቱ አያስደንቅም። “ከዚህ በኋላ በሰማይ:- ሃሌ ሉያ፣ በዝሙትዋ ምድርን ያጠፋችይቱን ታላቂቱን ጋለሞታ ስለ ፈረደባት፣ የባሪያዎቹንም ደም ከእጅዋ ስለ ተበቀለ፣ ፍርዶቹ እውነትና ጽድቅ ናቸውና ማዳንና ክብር ኃይልም የአምላካችን ነው ብሎ ሲናገር እንደ ብዙ ሕዝብ ታላቅ ድምፅ ያለ ድምፅን ሰማሁ። ደግመውም ሃሌ ሉያ አሉ፤ ጢስዋም ከዘላለም እስከ ዘላለም ይወጣል።”—ራእይ 19:1-3
-
-
ያህን ስለ ፍርዶቹ አወድሱት!ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
3. ታላቂቱ ጋለሞታ ሊፈረድባት የሚገባው ለምንድን ነው?
3 ታላቂቱ ባቢሎን ይህን የመሰለ ፍርድ ልትቀበል የሚገባት ለምንድን ነው? ይሖዋ ለኖህና በኖህም በኩል ለሰው ልጅ በሙሉ በሰጠው ሕግ መሠረት ደም አለአግባብ ማፍሰስ በሞት የሚያስቀጣ ወንጀል ነው። ይህ ሕግ ይሖዋ ለእሥራኤላውያን በሰጠው ሕግም በድጋሚ ተጠቅሶአል። (ዘፍጥረት 9:6፤ ዘኍልቁ 35:20, 21) ከዚህም በላይ በሙሴ ሕግ መሠረት ሥጋዊም ሆነ መንፈሳዊ ምንዝር በሞት የሚያስቀጣ በደል ነበር። (ዘሌዋውያን 20:10፤ ዘዳግም 13:1-5) ታላቂቱ ባቢሎን በሺህ ለሚቆጠሩ ዓመታት ደም ስታፈስስ ኖራለች። በተጨማሪም የአመንዝሮች ሁሉ እናት ነች። ለምሳሌ ያህል የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ቀሳውስትዋ እንዳያገቡ መከልከልዋ ብዙዎቹ ቀሳውስት ከባድ የሥነ ምግባር ብልግና እንዲፈጽሙ ምክንያት ሆኖአቸዋል። ከእነዚህም መካከል የኤድስ በሽታ የያዛቸው ጥቂቶች አይደሉም። (1 ቆሮንቶስ 6:9, 10፤ 1 ጢሞቴዎስ 4:1-3) ይሁን እንጂ ‘እስከ ሰማይ እስኪደርስ ድረስ የተከመረባት ኃጢአት’ በመንፈሳዊ አመንዝራነት የፈጸመችው ነው። የሐሰት ትምህርት ስታስተምር ኖራለች፣ ከምግባረ ብልሹ ፖለቲከኞችም ጋር ራስዋን አስተባብራለች። (ራእይ 18:5) ለሠራችው ወንጀል ሁሉ የሚገባትን መቀጫ የምትቀበልበት ጊዜ ስለ ደረሰ በሰማይ የነበሩት እጅግ ብዙ መዘምራን ለሁለተኛ ጊዜ ሃሌ ሉያ በማለት አስተጋቡ።
-