-
ያህን ስለ ፍርዶቹ አወድሱት!ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
1. ዮሐንስ ‘በሰማይ እንደ ብዙ ሕዝብ ድምፅ ሲናገር የሰማው’ ምንድን ነው?
ከዚያ በኋላ ታላቂቱ ባቢሎን አትኖርም! እንዲህ ያለው ዜና በጣም ያስደስታል። ዮሐንስም በሰማይ የደስታ ውዳሴ ድምፅ መስማቱ አያስደንቅም። “ከዚህ በኋላ በሰማይ:- ሃሌ ሉያ፣ በዝሙትዋ ምድርን ያጠፋችይቱን ታላቂቱን ጋለሞታ ስለ ፈረደባት፣ የባሪያዎቹንም ደም ከእጅዋ ስለ ተበቀለ፣ ፍርዶቹ እውነትና ጽድቅ ናቸውና ማዳንና ክብር ኃይልም የአምላካችን ነው ብሎ ሲናገር እንደ ብዙ ሕዝብ ታላቅ ድምፅ ያለ ድምፅን ሰማሁ። ደግመውም ሃሌ ሉያ አሉ፤ ጢስዋም ከዘላለም እስከ ዘላለም ይወጣል።”—ራእይ 19:1-3
2. (ሀ) “ሃሌ ሉያ” ማለት ምን ማለት ነው? በዚህ ጊዜ ላይ ዮሐንስ ሁለት ጊዜ ሃሌ ሉያ ሲባል መስማቱ ምን ያመለክታል? (ለ) ታላቂቱ ባቢሎን በመጥፋትዋ ክብር የሚሰጠው ማን ነው? አብራራ።
2 በእውነትም ሃሌ ሉያ! ሃሌ ሉያ ማለት “ያህን አወድሱ” ማለት ነው። “ያህ” ይሖዋ የተባለው መለኮታዊ ስም ምህጻረ ቃል ነው። እዚህ ላይ “እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን [“ይሖዋን፣” NW] ያመስግን፣ ሃሌ ሉያ” የሚለውን የመዝሙራዊውን ማሳሰቢያ ለማስታወስ እንገደዳለን። (መዝሙር 150:6) ዮሐንስ በዚህ ጊዜ በሰማይ የነበረው የመዘምራን ጓድ “ሃሌ ሉያ” እያለ ሁለት ጊዜ የውዳሴ ዝማሬ ሲያሰማ መስማቱ የመለኮታዊው እውነት መገለጥ ተከታታይነት እንዳለው ያሳያል። የግሪክኛ ቅዱሳን ጽሑፎች አምላክ ቀደም ካሉት የዕብራይስጥ ቅዱሳን ጽሑፎች አምላክ የተለየ አይደለም። ስሙም ይሖዋ ነው። የጥንትዋን ባቢሎን እንድትወድቅ ያደረገው አምላክ አሁን ደግሞ በታላቂቱ ባቢሎን ላይ ፈርዶ አጥፍቶአታል። ይህን በማድረጉ ክብር ሁሉ ሊሰጠው ይገባል። ታላቂቱ ባቢሎን የምትወድምበትን ሁኔታ ያመቻቸው ኃይል ከይሖዋ የመጣ ነው እንጂ እርሱ መሣሪያ አድርጎ ከተጠቀመባቸው ብሔራት ብቻ የመጣ አይደለም። ማዳን የሚቻለው ይሖዋ ብቻ ነው።—ኢሳይያስ 12:2፤ ራእይ 4:11፤ 7:10, 12
-
-
ያህን ስለ ፍርዶቹ አወድሱት!ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
4. ከታላቂቱ ባቢሎን የሚወጣው ጢስ “ከዘላለም እስከ ዘላለም” መጤሱ ምን ያመለክታል?
4 ታላቂቱ ባቢሎን በጠላት ኃይል እንደተወረረች ከተማ በእሳት ተያይዛለች። ከእርስዋም የሚወጣው ጢስ “ከዘላለም እስከ ዘላለም ይወጣል።” አንድ ከተማ በወራሪ ጠላት እጅ ወድቆ ሲቃጠል የቃጠሎው አመድ ትኩስ እስከሆነ ድረስ ጢስ መውጣቱ አይቀርም። ጢሱ ሳይቆም ከተማውን መልሶ ለመገንባት የሚሞክር ሰው በተዳፈነው ፍም ይቃጠላል። ከታላቂቱ ባቢሎን የሚወጣው ጢስም የተፈጸመባት ፍርድ የመጨረሻና የማያዳግም መሆኑን ለማመልከት “ከዘላለም እስከ ዘላለም” ስለሚወጣ ይህችን ነውረኛ ከተማ መልሶ ሊገነባ የሚችል ማንም አይኖርም። የሐሰት ሃይማኖት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ጠፍቶአል። በእርግጥም፣ ሃሌ ሉያ!—ከኢሳይያስ 34:5, 9, 10 ጋር አወዳድር።
-