-
ተዋጊው ንጉሥ አርማጌዶን ላይ ድል ይቀዳጃልራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
22. ዮሐንስ የመጨረሻውን ጦርነት ሂደት አጠቃልሎ የገለጸው እንዴት ነው?
22 ዮሐንስ የጦርነቱን የመጨረሻ ሂደት ሲያጠቃልል እንዲህ ይላል:- “በፈረሱም የተቀመጠውን ጭፍራዎቹንም ይወጉ ዘንድ አውሬውና የምድር ነገሥታት ጭፍራዎቻቸውም ተከማችተው አየሁ። አውሬውም ተያዘ በእርሱም ፊት ተአምራትን እያደረገ የአውሬውን ምልክት የተቀበሉትን ለምስሉም የሰገዱትን ያሳተ ሐሰተኛው ነቢይ ከእርሱ ጋር ተያዘ፤ ሁለቱም በሕይወት ሳሉ በዲን ወደሚቃጠል ወደ እሳት ባሕር ተጣሉ። የቀሩትም በፈረስ ላይ ከተቀመጠው ከአፉ በሚወጣው ሰይፍ ተገደሉ፣ ወፎችም ሁሉ ከሥጋቸው ጠገቡ።”—ራእይ 19:19-21
-
-
ተዋጊው ንጉሥ አርማጌዶን ላይ ድል ይቀዳጃልራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
-
-
25. (ሀ) በፈረሱ ላይ በተቀመጠው “ረዥም ሰይፍ የሚገደሉት” እነማን ናቸው? (ለ) “ከሚገደሉት” መካከል ትንሣኤ የሚያገኙ ይኖራሉ ብለን ለማሰብ እንችላለንን?
25 የመንግሥት ክፍል ባይሆኑም ይህን ብልሹ የሰው ልጆች ዓለም የሙጥኝ ያሉ ሁሉ “በፈረስ ላይ ከተቀመጠው ከአፉ በሚወጣው ሰይፍ ተገደሉ።” ኢየሱስ ሞት የሚገባቸው እንደሆኑ አድርጎ ይፈርድባቸዋል። እነዚህ ሰዎች ወደ እሳት ባሕር እንደሚጣሉ አለመነገሩ ትንሣኤ ይኖራቸዋል ብለን እንድናስብ ምክንያት ይሆነናልን? በዚያ ጊዜ በይሖዋ ፈራጅ የሚገደሉት ትንሣኤ እንደሚኖራቸው የተገለጸበት አንድም ቦታ አናገኝም። ኢየሱስ ራሱ እንደተናገረው “በጎች” ያልሆኑት ሁሉ ‘ለዲያብሎስና ለመላእክቱ ወደተዘጋጀው የዘላለም እሳት’ ይጣላሉ። ይህም ማለት ወደ ‘ዘላለም ጥፋት’ ይጣላሉ ማለት ነው። (ማቴዎስ 25:33, 41, 46) ይህ እርምጃ ‘አምላክ የለሽ ሰዎች የሚጠፉበት የፍርድ ቀን’ የመጨረሻ ክንውን ይሆናል።—2 ጴጥሮስ 3:7፤ ናሆም 1:2, 7-9፤ ሚልክያስ 4:1
-