የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • የእባቡን ጭንቅላት መቀጥቀጥ
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • 3. ዮሐንስ ሰይጣን ምን እንደሚደረግ ይነግረናል?

      3 ይሁን እንጂ ለሰይጣንና ለዘሮቹ የተጠበቀላቸው ነገር ምንድን ነው? ዮሐንስ እንደሚከተለው በማለት ይነግረናል:- “የጥልቁንም መክፈቻና ታላቁን ሰንሰለት በእጁ የያዘ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ። የቀደመውንም እባብ ዘንዶውን እርሱም ዲያብሎስና ሰይጣን የተባለውን ያዘው። ሺህ ዓመትም አሰረው፣ ወደ ጥልቅም ጣለው አሕዛብንም ወደ ፊት እንዳያስት ሺህ ዓመት እስኪፈጸም ድረስ በእርሱ ላይ ዘግቶ ማኅተም አደረገበት፤ ከዚያም በኋላ ለጥቂት ጊዜ ይፈታ ዘንድ ይገባዋል።”—ራእይ 20:1-3

  • የእባቡን ጭንቅላት መቀጥቀጥ
    ራእይ—ታላቁ መደምደሚያው ደርሷል!
    • 5. የጥልቁ መልአክ ሰይጣን ዲያብሎስን ምን ያደርገዋል? ለምንስ?

      5 ታላቁ ቀይ ዘንዶ ከሰማይ በተጣለ ጊዜ “ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ” ተብሎ ተጠርቶ ነበር። (ራእይ 12:3, 9) አሁን ደግሞ ተይዞ ወደ ጥልቁ የሚጣልበት በደረሰበት በዚህ ጊዜ ‘የቀደመው እባብ ዘንዶው፣ እርሱም ዲያብሎስና ሰይጣን’ በመባል ምንነቱ ሙሉ በሙሉ ተገልጾአል። ይህ ስመ ጥፉ የሆነ መዋጥን የሚወድ፣ አሳች፣ ስም አጥፊና ተቃዋሚ በሰንሰለት ታሥሮ በተዘጋውና በታሸገው ‘ጥልቅ ውስጥ’ ይጣላል። ይህም የሆነው ‘ከእንግዲህ ወዲህ አሕዛብን እንዳያስት’ ነው። ሰይጣን በጥልቁ ውስጥ ታስሮ በሚቆይበት በዚህ የሺህ ዓመት ጊዜ በጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ እንደተጣለ እሥረኛ በሰው ልጆች ላይ ምንም ዓይነት ተጽዕኖ አይኖረውም። የጥልቁ መልአክ ሰይጣንን ከጽድቅ መንግሥቱ ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት እንዳይኖረው ሙሉ በሙሉ ያገልለዋል። ለሰው ልጆች ታላቅ እፎይታ ይሆናል።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ