የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w18 ኅዳር ገጽ 31
  • የአንባቢያን ጥያቄዎች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የአንባቢያን ጥያቄዎች
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2018
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ማውጣት የሚቻለው እንዴት ነው?
    ተጨማሪ ርዕሰ ጉዳዮች
  • የጥንቷ ኢየሩሳሌም የጠፋችው መቼ ነው?​—ክፍል አንድ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2011
  • የጊዜ ቅደም ተከተል
    መጽሐፍ ቅዱስ—የያዘው መልእክት ምንድን ነው?
  • ሁለት ተቀናቃኝ ነገሥታት
    የዳንኤልን ትንቢት በትኩረት ተከታተል!
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2018
w18 ኅዳር ገጽ 31

የአንባቢያን ጥያቄዎች

ኢየሱስ ከመሞቱ በፊት በነበረው ምሽት “በጎ አድራጊዎች” በማለት የገለጻቸው ሰዎች እነማን ነበሩ? ይህ የማዕረግ ስም የተሰጣቸውስ ለምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ ዘመን የነበረ አንድ በጎ አድራጊ

ኢየሱስ ከመሞቱ በፊት በነበረው ምሽት ሐዋርያቱን በእምነት ባልንጀሮቻቸው መካከል የክብር ቦታ ለማግኘት መጣጣር እንደሌለባቸው መክሯቸዋል። እንዲህ ብሏቸዋል፦ “የአሕዛብ ነገሥታት በእነሱ ላይ ሥልጣናቸውን ያሳያሉ፤ እንዲሁም በሕዝባቸው ላይ ሥልጣን ያላቸው ሰዎች በጎ አድራጊዎች ተብለው ይጠራሉ። እናንተ ግን እንዲህ አትሁኑ።”—ሉቃስ 22:25, 26

ኢየሱስ በጎ አድራጊዎች በማለት የገለጻቸው ሰዎች እነማን ናቸው? በድንጋይ ላይ የተቀረጹ ጽሑፎች፣ ሳንቲሞችና በእጅ የተጻፉ ጽሑፎች እንደሚያሳዩት በግሪካውያንና በሮማውያን ማኅበረሰቦች ዘንድ ዝነኛ ሰዎችንና ገዢዎችን ለማክበር ዩዌርጊቲስ ወይም በጎ አድራጊ የሚል የማዕረግ ስም መስጠት የተለመደ ነገር ነበር። እነዚህ ሰዎች ይህ የማዕረግ ስም የሚሰጣቸው ሕዝቡን የሚጠቅሙ አንዳንድ ተግባሮችን ስላከናወኑ ነው።

በርካታ ነገሥታት በጎ አድራጊ የሚል ማዕረግ ተሰጥቷቸዋል። ከእነዚህ መካከል ሣልሳዊ ቶሌሚ (ከ247-222 ዓ.ዓ. ገደማ) እና ቶሌሚ ስምንተኛ (ከ147-117 ዓ.ዓ. ገደማ) የተባሉት የግብፅ ገዢዎች ይገኙበታል። በተጨማሪም ሮማዊ ገዢዎች የሆኑት ጁሊየስ ቄሳር (48-44 ዓ.ዓ.) እና አውግስጦስ (31 ዓ.ዓ.–14 ዓ.ም.) እንዲሁም የይሁዳ ንጉሥ የነበረው ታላቁ ሄሮድስ በዚህ የማዕረግ ስም ተጠርተዋል። ሄሮድስ ይህን የማዕረግ ስም ያገኘው ረሃብ በተከሰተበት ወቅት ሕዝቡን ለመታደግ ስንዴ ከውጭ አገር ስላስመጣና ለችግረኞች ልብስ ስለሰጠ ሳይሆን አይቀርም።

ጀርመናዊው የመጽሐፍ ቅዱስ ምሁር አዶልፍ ዲስማን እንደገለጹት በጎ አድራጊ የሚለው የማዕረግ ስም በስፋት ይሠራበት ነበር። እንዲህ ብለዋል፦ “በድንጋይ ላይ ከተቀረጹ ጽሑፎች መካከል ብንፈልግ [ይህ የማዕረግ ስም የተጠቀሰባቸውን] ከመቶ የሚበልጡ ቦታዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ማግኘት እንችላለን።”

ታዲያ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ “እናንተ ግን እንዲህ አትሁኑ” ሲላቸው ምን ማለቱ ነበር? ለማኅበረሰቡ ችግር ደንታ ቢሶች እንዲሆኑ ማለትም በዙሪያቸው ስላለው ሕዝብ ደህንነት እንዳያስቡ እየነገራቸው ነበር? በጭራሽ። ኢየሱስን ያሳሰበው የልግስና ድርጊት ለመፈጸም የሚነሳሱበት ዓላማ መሆን አለበት።

በኢየሱስ ዘመን የነበሩ ባለጸጋ ሰዎች በስፖርት ውድድር ቦታዎች ለሚቀርቡ ትርኢቶችና ጨዋታዎች የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ፣ መናፈሻዎችንና ቤተ መቅደሶችን በመገንባት እንዲሁም እንዲህ ያሉ ሌሎች እንቅስቃሴዎችን በመደገፍ ጥሩ ስም ለማትረፍ ይሞክሩ ነበር። ሆኖም ዓላማቸው አድናቆትና ተወዳጅነት ማትረፍ ወይም በምርጫ ወቅት ብዙ ሰው እንዲመርጣቸው ማድረግ ነበር። አንድ የማመሣከሪያ ጽሑፍ “ከእነዚህ ሰዎች መካከል ከልባቸው ተነሳስተው ልግስና የሚያሳዩ ሰዎች ቢኖሩም የአብዛኞቹ ዓላማ ግን ፖለቲካዊ ጥቅም ማግኘት ነበር” በማለት ይገልጻል። ኢየሱስ ተከታዮቹን ያሳሰባቸው እንዲህ ያለውን ከፍ ያለ ቦታ ላይ የመድረስ ፍላጎትና የግል ጥቅምን የማራመድ ዝንባሌ እንዲያስወግዱ ነበር።

ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ሐዋርያው ጳውሎስ፣ ለመስጠት የምንነሳሳበትን ትክክለኛ ዓላማ አስመልክቶ ሲጽፍ ይህን አስፈላጊ እውነት ጎላ አድርጎ ገልጿል። በቆሮንቶስ ለነበሩ የእምነት ባልንጀሮቹ “አምላክ በደስታ የሚሰጠውን ሰው ስለሚወድ እያንዳንዱ ሰው ቅር እያለው ወይም ተገዶ ሳይሆን በልቡ ያሰበውን ይስጥ” በማለት ጽፎላቸዋል።—2 ቆሮ. 9:7

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ