የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w18 መጋቢት ገጽ 13
  • የአንባቢያን ጥያቄዎች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የአንባቢያን ጥያቄዎች
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2018
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የጳውሎስን ምሳሌ በመከተል መንፈሳዊ እድገት አድርጉ
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2008
  • ‘ከሰው ሁሉ ደም ንጹሕ ነኝ’
    ‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
  • “በሚገባ . . . መመሥከር”
    ‘ስለ አምላክ መንግሥት በሚገባ መመሥከር’
  • አትፍራ፣ ይሖዋ ረዳትህ ነው
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2018
w18 መጋቢት ገጽ 13
ሐዋርያው ጳውሎስ

የአንባቢያን ጥያቄዎች

የይሖዋ ምሥክሮች ሐዋርያው ጳውሎስን ራሰ በራ እንደሆነ አድርገው የሚሥሉት ለምንድን ነው?

እውነቱን ለመናገር በዛሬው ጊዜ ማንም ሰው ስለ ጳውሎስ መልክ በእርግጠኝነት መናገር አይችልም። በጽሑፎቻችን ላይ የሚቀርቡት ሥዕሎች፣ ጳውሎስን ለመግለጽ የገቡ ሥዕላዊ መግለጫዎች ናቸው እንጂ በተረጋገጡ አርኪኦሎጂያዊ ማስረጃዎች ላይ የተመሠረቱ አይደሉም።

ይሁንና የጳውሎስ መልክ ምን ሊመስል እንደሚችል የሚጠቁሙ አንዳንድ መረጃዎች አሉ። ለምሳሌ ያህል፣ የጽዮን መጠበቂያ ግንብ የመጋቢት 1, 1902 እትም እንዲህ ይላል፦ “የጳውሎስን መልክ በተመለከተ፦ . . . በ150 ዓ.ም. ገደማ በተዘጋጀ ‘አክትስ ኦቭ ፖል ኤንድ ቴክላ’ የተሰኘ . . . ጽሑፍ ላይ ስለ ጳውሎስ የሚገልጽ ለዘመናት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣና ምናልባትም ከሁሉ የተሻለ ሐሳብ ይገኛል። በዚህ ጽሑፍ ላይ ጳውሎስ ‘ቁመቱ አጭር፣ ራሰ በራ፣ እግረ ወረሃ እና ፈርጣማ ሰውነት ያለው፣ ቅንድቦቹ የገጠሙ፣ አፍንጫው ረጅም’ እንደሆነ ተደርጎ ተገልጿል።”

ዚ ኦክስፎርድ ዲክሽነሪ ኦቭ ዘ ክርስቺያን ቸርች (የ1997 እትም) “‘ዚ አክትስ ኦቭ ፖል ኤንድ ቴክላ’ ከያዛቸው ሐሳቦች አንዳንዶቹ ከታሪክ አንጻር ጨርሶ እውነት አይደሉም ማለት አይቻልም’ ይላል። ዚ አክትስ ኦቭ ፖል ኤንድ ቴክላ የተሰኘው ጥንታዊ ጽሑፍ፣ ከተዘጋጀ በኋላ በነበሩት ጥቂት መቶ ዓመታት ትልቅ ቦታ ይሰጠው ነበር፤ በአሁኑ ጊዜ 80 የሚያህሉ የዚህ መጽሐፍ ጥንታዊ የግሪክኛ ቅጂዎች መኖራቸውና ወደ ሌሎች ቋንቋዎችም መተርጎሙ ለዚህ ማስረጃ ይሆናል። በመሆኑም በጽሑፎቻችን ላይ የሚወጡት ሥዕላዊ መግለጫዎች፣ አንዳንድ ጥንታዊ ጽሑፎች የሐዋርያው ጳውሎስ መልክ ምን ይመስል እንደነበር ከሚሰጡት ሐሳብ ጋር ይስማማሉ።

ሆኖም ከጳውሎስ ጋር በተያያዘ፣ ከመልኩ የበለጠ ትልቅ ቦታ ሊሰጣቸው የሚገቡ ሌሎች ነገሮች እንዳሉ መገንዘብ አስፈላጊ ነው። ጳውሎስ አገልግሎቱን እያከናወነ በነበረበት ጊዜም ሥጋዊ አስተሳሰብ ያላቸው አንዳንድ ሰዎች “በመካከላችን በአካል ሲገኝ . . . ደካማ ከመሆኑም በላይ ንግግሩ የተናቀ ነው” በማለት ተችተውት ነበር። (2 ቆሮ. 10:10) ይሁን እንጂ ጳውሎስ ክርስቲያን የሆነው ኢየሱስ ራሱ በተአምራዊ መንገድ ስለተገለጠለት መሆኑን ልንዘነጋ አይገባም። በተጨማሪም ጳውሎስ “በአሕዛብ . . . ፊት [የኢየሱስን ስም] እንዲሸከም [ለክርስቶስ] የተመረጠ ዕቃ” በመሆን ያከናወነውን ሥራ ማሰብ እንችላለን። (ሥራ 9:3-5, 15፤ 22:6-8) ከዚህም ሌላ ጳውሎስ በይሖዋ መንፈስ መሪነት ከጻፋቸው የመጽሐፍ ቅዱስ መጻሕፍት ምን ያህል ጥቅም እንደምናገኝ አንርሳ።

ሐዋርያው ጳውሎስ

ጳውሎስ ክርስቲያን ከመሆኑ በፊት ስላከናወናቸው ነገሮች በትምክህት አልተናገረም፤ ስለ መልክና ቁመናውም ቢሆን የገለጸው ነገር የለም። (ሥራ 26:4, 5፤ ፊልጵ. 3:4-6) እንዲያውም “ከሐዋርያት ሁሉ የማንስና ሐዋርያ ተብዬ ልጠራ የማይገባኝ ነኝ” በማለት ተናግሯል። (1 ቆሮ. 15:9) ከጊዜ በኋላም “ከቅዱሳን ሁሉ ለማንስ ለእኔ ይህ ጸጋ ተሰጠኝ፤ ይህም ሊደረስበት ስለማይችለው የክርስቶስ ብልጽግና የሚገልጸውን ምሥራች ለአሕዛብ እንዳውጅ [ነው]” በማለት ጽፏል። (ኤፌ. 3:8) ይህ ምሥራች ከጳውሎስ መልክ ይበልጥ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ጥርጥር የለውም።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ