የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • የደብዳቤ አጻጻፍ
    ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት መመሪያ መጽሐፍ
    • ይገኛል። የይሖዋ ሥራ ግን የይሖዋ በረከት ስላለው በአስደናቂ ሁኔታ በመስፋፋት ላይ ይገኛል። ወንድሞችህ በአካባቢህ በመከናወን ላይ ስለሚገኘው ቲኦክራሲያዊ ዕድገት ሲሰሙ በጣም ደስ ይላቸዋል። ምንም ዓይነት ሰው ብትሆን የአንተ ሞቅ ያለና ግላዊ አሳቢነት የተገለጸበት ደብዳቤ ቢደርሳቸው ደስ የሚሰኙ ሰዎች ይኖራሉ። ይህን የመሰለውን ለሌሎች የማሰብ ባሕርይ ማሳየት ደግሞ የአገልግሎታችን ክፍል ነው፤ ምክንያቱም የወንድማማች ፍቅራችን በቦታ ስለተራራቅን ብቻ መቋረጥ አይኖርበትም። ደብዳቤ በመጻጻፍ ሊጠናከር ይችላል።

  • መልሶችህን ማሻሻል
    ቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት መመሪያ መጽሐፍ
    • ጥናት 18

      መልሶችህን ማሻሻል

      1, 2. ሁላችንም ጥሩ መልስ ለመስጠት ጥረት ማድረግ የሚኖርብን ለምንድን ነው?

      1 ክርስቲያኖች በሙሉ ጥሩ መልስ የመስጠት ችሎታቸውን ማዳበር ይኖርባቸዋል። ሐዋርያው ጳውሎስ “ለእያንዳንዱ እንዴት እንድትመልሱ እንደሚገባችሁ ታውቁ ዘንድ ንግግራችሁ ሁልጊዜ፣ በጨው እንደተቀመመ በጸጋ ይሁን” ሲል ጽፏል። (ቆላ. 4:6) መልሶቻችንን ለማሻሻል ጥረት ማድረጋችንም የተገባ ነገር ነው። ጥሩ መልስ ስንሰጥ ልባዊ ደስታ ይሰማናል። “ሰው በአፉ መልስ ደስ ይለዋል፣ ቃልም በጊዜው ምንኛ መልካም ነው!” — ምሳሌ 15:23

      2 በግልህ መልሶችህን ማሻሻል እንደሚያስፈልግህ ይሰማሃልን? በጉባኤ ስብሰባዎች ስላለህ ተሳትፎ ሙሉ እርካታ አለህ ወይስ ብታሻሽል በጣም ደስ የምትሰኝበት መስክ አለ? በመስክ አገልግሎትህ ባጋጠመህ ሁኔታ ከዚህ የተሻለ ማድረግ ይገባኝ ነበር ያልክበት ጊዜ ይኖራልን? ሁላችንም እንዲህ የሚሰማን ጊዜ ስለሚኖር መልሶቻችንን እንዴት ለማሻሻል እንደምንችል አብረን ብንመረምር ጥሩ ይሆናል።

      3, 4. በስብሰባ ላይ ለአንድ ጥያቄ የተለያዩ ሐሳቦች ሊሰጡ የሚችሉት እንዴት ነው?

      3 የጉባኤ ስብሰባዎች። በአብዛኞቹ የይሖዋ ምሥክሮች ስብሰባዎች አንዳንድ ግለሰቦች በመጠበቂያ ግንብ ጥናት ወይም በመጽሐፍ ጥናት ወይም በቲኦክራሲያዊ የአገልግሎት ትምህርት ቤት ክለሳ ለሚጠየቁ ጥያቄዎች ምን ጊዜም መልስ ለመስጠት ዝግጁ እንደሆኑ ይስተዋላል። ይህ በአጋጣሚ ያገኙት ችሎታ አይደለም። ለበርካታ ዓመታት ካደረጓቸው ጥናቶችና ከይሖዋ ሕዝቦች ጋር ባደረጓቸው ስብሰባዎች አማካኝነት ካካበቱት እውቀት የሚያገኙት መልስ ሊሆን ይችላል። ይሁን እንጂ አብዛኛውን ጊዜ የወቅቱን ጽሑፍ መዘጋጀታቸውም መልስ ለመስጠት ያበቃቸዋል። አዳዲሶች እንኳን የሚጠናውን ጽሑፍ ቀደም ብለው ካጠኑ ጥሩ መልስ ሊሰጡ ይችላሉ። — ሥራ 15:28

      4 በአንድ ጥያቄ ላይ መልስ ለመስጠት የመጀመሪያው ሰው ከሆንክ ወዲያና ወዲህ ሳትል ለጥያቄው ቀጥተኛ መልስ ብትሰጥ ጥሩ ይሆናል። ለጥያቄው መልስ ተሰጥቶበት ከነበረ ግን ውይይቱ በዚሁ ማብቃት ይኖርበታል ብለህ ማሰብ አይገባህም። በአንዱ ጥያቄ ላይ ተጨማሪ ሐሳብ ለመስጠት ከሚቀጥሉት አንዱን ለማድረግ ትችላለህ። መልሱን ሰፋ አድርጎ ማብራራት፣ በአንቀጹ ውስጥ የተጠቀሱ ጥቅሶች ለመልሱ እንዴት ድጋፍ እንደሚሰጡ መግለጽ ወይም ውይይት የሚደረግበት ነጥብ ሕይወታችንን እንዴት እንደሚነካ ማብራራት ይቻላል። ትምህርቱ ስለ ዓለም ሁኔታ ወይም ስለ ሐሰት ሃይማኖት ልማዶች የሚገልጽ ከሆነ በግል ስላጋጠመህ ተሞክሮ ወይም አንቀጹ የሚናገረው ነገር ትክክል መሆኑን የሚያረጋግጥ የአካባቢ ሁኔታ መናገር ትችላለህ። ይህም ውይይቱን ያዳብረዋል።

      5. በአጭሩና በራስ አነጋገር መልስ መስጠት ጥሩ የሚሆነው ለምንድን ነው?

      5 መልሶች አብዛኛውን ጊዜ አጭርና ነጥቡን የሚያስጨብጡ ሲሆኑ የበለጠ ክብደት ይኖራቸዋል፤ በሚያዳምጡት ሰዎች አእምሮ ውስጥም በይበልጥ ይቀረጻሉ። አብዛኛውን ጊዜ እንደነዚህ ያሉ መልሶች ቢሰጡ ጥሩ ነው። አንድ ግለሰብ የአንቀጹን ሐሳቦች በሙሉ ከላይ እስከ ታች የሚያነበንብ ከሆነ ፍሬ ሐሳቡ ጉልህ ሆኖ ስለማይታይ አድማጮች የጥያቄው መልስ ምን እንደሆነ መገንዘብ ያቅታቸዋል። በተጨማሪም መልስ ሰጪው በራሱ አነጋገር የሚሰጣቸው መልሶች ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖራቸዋል። በራስ አነጋገርና ቃላት መልስ መስጠት መልስ ሰጪው ትምህርቱን የራሱ እንዲያደርገው ያስችለዋል። አድማጮችም ያልተገነዘቡትን ሐሳብ እንዲያስተውሉ ይረዳቸዋል። ይህን ችሎታ በማዳበር ረገድ በአገልግሎት ትምህርት ቤት የምትሰጣቸው ንግግሮች ሊረዱህ ይችላሉ።

      6. ጥያቄ በሚጠየቅበት ጊዜ መልስ ለመስጠት ዝግጁ በመሆን ረገድ ልንሻሻል የምንችለው እንዴት ነው?

      6 መልስ ለመስጠት ዝግጁ በመሆን ረገድስ ልታሻሽል ትችላለህን? ለዚህም የቅድሚያ ዝግጅት ማድረግ አስፈላጊ ነው። ይሁን እንጂ አንቀጹ በሚነበብበት ጊዜ ወይም ሌሎች ሐሳብ በሚሰጡበት ጊዜ መዘጋጀት ተገቢ አይደለም፤ ምክንያቱም ከስብሰባው ማግኘት የሚገባህን ጥቅም ያሳጣሃል። በመልሶችህ ላይ ቀደም ብለህ ምልክት የማድረግ ልማድ ይኑርህ። ረዥም ሐረግ ወይም አረፍተ ነገር ሳይሆን ቁልፍ የሆኑ ጥቂት ቃላትን ብታሰምር እነዚህን ቁልፍ ቃላት መመልከት ብቻውን ሙሉውን ሐሳብ ለማስታወስ ስለሚያስችልህ መልስ ለመስጠት ዝግጁ ለመሆን ትችላለህ። የአንድ አንቀጽ ጥያቄ በ“ሀ” እና በ“ለ” የተከፈለ ከሆነ የትኛው ክፍል የ“ሀ” መልስ እንደሆነና የትኛው ክፍል የ“ለ” መልስ እንደሆነ በጽሑፉ ሕዳግ ላይ ብታመለክት ከጥናቱ መሪ ቀድመህ ሐሳብ እንዳትሰጥ ሊረዳህ ይችላል። ጽሑፉ የተዘጋጀ ጥያቄ ባይኖረውም እንኳን የአድማጮች ውይይት የሚደረግበት ከሆነ ቁልፍ ነጥብ ነው ብለህ የምታስበውን ብታሰምር ጠቃሚ ይሆናል። ይህን ማድረግህ ቅጽበታዊ መልስ ለመስጠትና ሕያው የሆነ ውይይት ለማድረግ ያስችልሃል። በአንድ ስብሰባ ላይ አንድ ጊዜ መልስ ከሰጠህ በኋላ ሌሎቹን መልሶች ለሌሎች መተው እንደሚገባህ ተሰምቶህ ዝም ማለት አይገባህም። በነፃነት ሐሳብ ለመስጠት ፈቃደኛ ሁን።

      7. በስብሰባዎች ላይ ሐሳብ የመስጠት ኃላፊነት እንዳለብን ሊሰማን የሚገባው ለምንድን ነው?

      7 አንዳንዶች ከእኔ የተሻለ መልስ ሊሰጡ የሚችሉ አሉ በማለትና በዓይነ አፋርነት መልስ ከመስጠት ወደኋላ ሊሉ ይችላሉ። ይሁን እንጂ መጽሐፍ ቅዱስ ሐሳባችንን ለሌሎች የማካፈል ኃላፊነት ያለብን መሆኑን እንድንገነዘብ ይመክረናል። ሐዋርያው ጳውሎስ እንደሚከተለው በማለት ጽፏል:- “እንዳይነቃነቅ የተስፋችንን ምስክርነት እንጠብቅ፤ ለፍቅርና ለመልካምም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በርሳችን እንተያይ፤ በአንዳንዶችም ዘንድ ልማድ እንደሆነው፣ መሰብሰባችንን አንተው። እርስ በርሳችን እንመካከር እንጂ።” (ዕብ. 10:23–25) መልስ ስንሰጥ ሌሎችን ለፍቅርና ለመልካም ሥራ እናነቃቃለን፣ እናበረታታቸዋለን፣ ልባቸውም በደስታ ሞቅ እንዲል እናደርጋለን። እኛም ብንሆን እንጠቀማለን። መስጠት የሚያስገኘውን ደስታ ለመቅመስ ስለምንችል በግላችን ማበረታቻ እናገኛለን።

      8–12. በመስክ አገልግሎት የሚያጋጥሙንን የተቃውሞ አስተያየቶች እንዴት መመለስ እንደምንችል አንዳንድ ሐሳቦች ስጥ።

      8 በመስክ አገልግሎት ለሚያጋጥሙት የተቃውሞ አስተያየቶች መልስ መስጠት። አዘውትረህ የግል ጥናት የምታደርግና ዘወትር በስብሰባዎች የምትገኝ ከሆነ ከቤት ወደ ቤት በምታደርገው አገልግሎት ለሚያጋጥሙህ ጥያቄዎች መልስ መስጠት እንደማያዳግትህ ትገነዘባለህ። ይሁን እንጂ የተጠየቅከውን ጥያቄ መልስ የማታውቅ ከሆነ አለማወቅህን ለጠያቂው ለመናገር ማመንታት አይገባህም። ማብራሪያ ይዘህ እንደምትመለስ ንገረው። ሰውዬው ቅን ከሆነ እንደዚያ ብታደርግ ቅር አይለውም።

      9 እንደነዚህ ካሉት ጥያቄዎች ሌላ የተቃውሞ አስተያየት ሊያጋጥምህ ይችላል። እንዴት ልትመልስ ትችላለህ? ለተቃውሞ አስተያየቱ መልስ ከመስጠትህ በፊት ስለ ሰውዬው አስተሳሰብ የምታውቀው ነገር ቢኖር ይጠቅምሃል። እንዲህ ብሎ እንዲናገር ያስቻለው ነገር ምን እንደሆነ ልትጠይቀው ትችላለህ። ለምሳሌ ያህል አንድ ሰው በክርስቶስ እንደማታምኑ ሰምቼአለሁ ሊል ይችላል። ይሁን እንጂ ሰውዬውን ግራ ያጋባው በሥላሴ መሠረተ ትምህርት ላይ ያለው እምነት ነው። ብዙ የተቃውሞ አስተያየቶች የሚሰነዘሩት እንደዚህ ባለው ግራ መጋባት ምክንያት ነው። ውይይት ከመጀመር በፊት ቁልፍ ስለሆኑ ቃላት መግባባት ላይ መድረስ በጣም አስፈላጊ ነው። ይህ ብቻውን ለተቃውሞ አስተያየቱ መልስ ይሆንና በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ውይይት ማድረግ አስፈላጊ ላይሆን ይችላል።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ