-
ለማንበብ ትጋመጠበቂያ ግንብ—1996 | ግንቦት 15
-
-
ሩት “ለኑኃሚን” ከቦዔዝ ወንድ ልጅ ወለደችላት። ሩት የዳዊት በኋላም የኢየሱስ ክርስቶስ ቅድመ ዓያት ሆናለች። በዚህ መንገድ ‘ፍጹም ደመወዝ’ አገኘች። ከዚህም በላይ ይህን ቅዱስ ጽሑፋዊ ታሪክ የሚያነቡ ሁሉ ከይሖዋ ጋር በታማኝነት ከተጣበቅን አብዝቶ እንደሚባርከን የሚያሳይ ጠቃሚ ትምህርት ያገኛሉ።—ሩት 2:12፤ 4:17-22፤ ምሳሌ 10:22፤ ማቴዎስ 1:1, 5, 6
16. ሦስቱ ዕብራውያን የገጠማቸው ፈታኝ ሁኔታ ምን ነበር? ይህ ታሪክ እኛን እንዴት ሊጠቅመን ይችላል?
16 ሲድራቅ፣ ሚሳቅና አብደናጎ የተባሉት ዕብራውያን ያስመዘገቡት ታሪክ ፈታኝ ሁኔታዎች ሲያጋጥሙን በአምላክ ዘንድ የታመንን ትእዛዝ አክባሪዎች እንድንሆን ሊረዳን ይችላል። ዳንኤል ምዕራፍ 3 ሲነበብ ሁኔታውን በዓይነ ሕሊናችሁ ተመልከቱ። ባቢሎናውያን ባለ ሥልጣኖች በተሰበሰቡበት በዱራ ሜዳ አንድ በጣም ግዙፍ የወርቅ ምስል ቆሟል። የሙዚቃ መሣሪያዎች ድምፅ ሲሰማ ንጉሥ ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ወድቀው ይሰግዳሉ። ከሲድራቅ፣ ሚሳቅና አብደናጎ በቀር ሁሉም ለምስሉ ሰግደዋል። የእርሱን አማልክት እንደማያገለግሉና ለወርቁ ምስል እንደማይሰግዱ አክብሮት በተሞላበት መንገድ ፈርጠም ብለው ለንጉሡ ተናገሩ። እነዚህ ወጣት ዕብራውያን በኃይል የሚንቀለቀል እሳት በሚነድበት እቶን ውስጥ ተጣሉ። ይሁን እንጂ የተፈጸመው ሁኔታ ምን ነበር? ንጉሡ ወደ እሳቱ ውስጥ ሲመለከት አራት ሰዎች አየ፤ አንደኛው “የአማልክት ልጅ” ይመስል ነበር። (ዳንኤል 3:25) ሦስቱ ዕብራውያን ከእቶኑ ውስጥ እንዲወጡ ተደረገ፤ ናቡከደነፆርም አምላካቸውን ባረከ። ይህን ታሪክ በዓይነ ሕሊና መመልከት የሚያስደስት ነው። በፈተና ወቅት ለይሖዋ የታመኑ ትእዛዝ አክባሪ ሆኖ በመገኘት ረገድ ትልቅ ትምህርት የሚሰጥ ታሪክ ነው!
መጽሐፍ ቅዱስን በቤተሰብ መልክ በማንበብ ጥቅም ማግኘት
17. ቤተሰባችሁ መጽሐፍ ቅዱስን አንድ ላይ በማንበብ ሊማራቸው ከሚችላቸው ጠቃሚ ነገሮች መካከል አንዳንዶቹን በአጭሩ ጥቀስ።
17 ዘወትር መጽሐፍ ቅዱስን አብራችሁ የምታነቡ ከሆነ ቤተሰባችሁ ብዙ ጥቅም ሊያገኝ ይችላል። ከዘፍጥረት ጀምራችሁ ስታነቡ የፍጥረት ሥራዎችን በዓይነ ሕሊናችሁ መዳሰስና በሰው ልጅ የመጀመሪያ መኖሪያ በገነት የነበረውን ሁኔታ በጥልቀት መመልከት ትችላላችሁ። የታመኑ የዕብራውያን አባቶችና ቤተሰቦቻቸው ያሳለፉትን ተሞክሮ መካፈልና እስራኤላውያን ቀይ ባሕርን በደረቅ ምድር ሲሻገሩ መመልከት ትችላላችሁ። እረኛ የነበረው ብላቴናው ዳዊት ግዙፉን ፍልስጤማዊ ጎልያድን ሲጥለው ታያላችሁ። ቤተሰባችሁ የይሖዋ ቤተ መቅደስ በኢየሩሳሌም ሲገነባ፣ በባቢሎናውያን ጭፍራ ሲደመሰስና በገዥው በዘሩባቤል መሪነት ተመልሶ ሲገነባ ሁኔታው ምን ይመስል እንደነበር መመልከት ይችላል። መላእክት የኢየሱስን መወለድ ሲያበስሩ በቤተ ልሔም አቅራቢያ ከነበሩት ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ከነበራቸው እረኞች ጋር አብራችሁ መስማት ትችላላችሁ። ስለ ጥምቀቱና አገልግሎቱ ዝርዝር ታሪኮችን ማግኘት ትችላላችሁ፤ ሕይወቱን ቤዛ አድርጎ ሲሰጥ መመልከትና በትንሣኤ መነሣቱ ባስገኘው ደስታ መካፈል ትችላላችሁ። በመቀጠልም ከሐዋርያው ጳውሎስ ጋር በመጓዝ ክርስትና እየተስፋፋ ሲሄድ የተቋቋሙትን ጉባኤዎች ማስተዋል ትችላላችሁ። ቤተሰባችሁ በራእይ መጽሐፍ ውስጥ የተገለጸውንና የክርስቶስን የሺህ ዓመት ግዛት የሚያካትተውን የሐዋርያው ዮሐንስ ታላቅ ራእይም መመልከት ይችላል።
18, 19. በቤተሰብ መልክ መጽሐፍ ቅዱስ ማንበብን በተመለከተ ምን ሐሳቦች ቀርበዋል?
18 መጽሐፍ ቅዱስን በቤተሰብ መልክ ድምፃችሁን እያሰማችሁ የምታነቡ ከሆነ ንባባችሁ ጥራትና ግለት ያለው ይሁን። አንዳንዶቹን የቅዱሳን ጽሑፎች ክፍል በምታነቡበት ጊዜ አንዱ የቤተሰብ አባል (ምናልባትም አባትየው ሊሆን ይችላል) እንደ ተራኪ ሆኖ አጠቃላይ ታሪኩን የሚዘግበውን ክፍል ሊያነብ ይችል ይሆናል። ሌሎቻችሁ ደግሞ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተገለጹትን ባለ ታሪኮች በመወከል ትክክለኛውን ስሜት በሚያንጸባርቅ መንገድ ልታነቡ ትችላላችሁ።
19 በቤተሰብ መልክ ሆናችሁ መጽሐፍ ቅዱስን ስታነቡ የንባብ ችሎታችሁ ሊሻሻል ይችላል። ስለ አምላክ ያላችሁ እውቀትም ሊጨምር ስለሚችል ይበልጥ ከእርሱ ጋር ያቀራርባችኋል። አሳፍ እንደሚከተለው ብሎ ዘምሯል፦ “ለእኔ ግን ወደ እግዚአብሔር መቅረቤ መልካም ነው፤ የእርሱን ሥራ ለማብሠር እንድችል እግዚአብሔር አምላክን መጠጊያዬ አድርጌአለሁ።” (መዝሙር 73:28 የ1980 ትርጉም) ይህም ቤተሰባችሁ ‘የማይታየውን [ይሖዋን] እንደሚታየው አድርጎ እንደጸናው’ እንደ ሙሴ እንዲሆን ይረዳዋል።—ዕብራውያን 11:27
ንባብና ክርስቲያናዊ አገልግሎት
20, 21. የመስበክ ተልእኮአችን ከማንበብ ችሎታ ጋር የተያያዘው እንዴት ነው?
20 “የማይታየውን” አምላክ ለማምለክ ያለን ፍላጎት ጥሩ አንባቢዎች ለመሆን እንድንጣጣር ሊያነሳሳን ይገባል። ጥሩ የማንበብ ችሎታ ከአምላክ ቃል ለመመሥከር ይረዳናል። ኢየሱስ “ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፣ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው” ባለ ጊዜ ለተከታዮቹ የሰጣቸውን የመንግሥቱን የስብከት ሥራ የማከናወን ተልእኮ ለመፈጸም እንደሚረዳን እሙን ነው። (ማቴዎስ 28:19, 20፤ ሥራ 1:8) የይሖዋ አገልጋዮች ዋነኛ ሥራ ምሥክርነት መስጠት ነው፤ የማንበብ ችሎታ ደግሞ ይህን ለማከናወን ይረዳናል።
21 ጥሩ አንባቢዎችና የተዋጣልን የአምላክ ቃል አስተማሪዎች ለመሆን ጥረት ማድረግ የግድ አስፈላጊ ነው። (ኤፌሶን 6:17) እንግዲያውስ ‘የእውነትን ቃል በትክክል የምትጠቀም ሆነህ የተፈተነውን ራስህን ለአምላክ ለማቅረብ ትጋ።’ (2 ጢሞቴዎስ 2:15) ለማንበብ ትጉዎች በመሆን ስለ ቅዱስ ጽሑፋዊ እውነት ያለህን እውቀትና የይሖዋ ምሥክር ሆነህ የማገልገል ብቃትህን አሳድግ።
-
-
የአምላክን ቃል አንብቡ በእውነትም አገልግሉትመጠበቂያ ግንብ—1996 | ግንቦት 15
-
-
የአምላክን ቃል አንብቡ በእውነትም አገልግሉት
“አቤቱ ይሖዋ ሆይ፣ መንገድህን አስተምረኝ። በእውነትህም እመላለሳለሁ።”—መዝሙር 86:11 አዓት
1. የዚህ መጽሔት የመጀመሪያ እትም እውነትን በተመለከተ የሰጠው ሐሳብ ምን ነበር?
ይሖዋ ብርሃንና እውነትን ይልካል። (መዝሙር 43:3) ከዚህም በተጨማሪ ቃሉን መጽሐፍ ቅዱስን የማንበብና እውነትን የመማር ችሎታ ሰጥቶናል። በሐምሌ 1879 የወጣው የዚህ መጽሔት የመጀመሪያ እትም እንደሚከተለው ብሎ ነበር፦ “እውነት በጣም ተንሰራፍቶ በሚገኝ የሐሰት አረም መካከል ልትዋጥ ምንም ያህል እንዳልቀራት በሕይወት ደን ውስጥ እንደምትገኝ ትንሽ አበባ ናት። ካገኘሃት በንቃት ልትከታተላት ይገባሃል። ውብ መሆኗን ከተገነዘብክ የሐሰትን አረምና የግትርነትን እሾህ ጠራርገህ ማጽዳት ይኖርብሃል። ንብረትህ ልታደርጋት ከፈለግህ ራስህን ዝቅ ማድረግ አለብህ። አንድ የእውነት አበባ ስላገኘህ ብቻ አትርካ። አንድ ብቻ ቢበቃ ኖሮ ሌላ ባልኖረም ነበር። መሰብሰብህን አታቋርጥ፣ ፍለጋህን ቀጥል።” የአምላክን ቃል ማንበብና ማጥናት ትክክለኛ እውቀት ለመቅሰምና በእውነት ለመመላለስ ያስችለናል።—መዝሙር 86:11 አዓት
-