-
ብሮሹሮችን በማበርከት ፍላጎት ያላቸውን ሰዎች ፈልጎ ማግኘትየመንግሥት አገልግሎት—1993 | ሐምሌ
-
-
ብሮሹሮችን በማበርከት ፍላጎት ያላቸውን ሰዎች ፈልጎ ማግኘት
1 ብሮሹሮች ኃይለኛ መሣሪያዎች ናቸው። 32 ገጾች ብቻ ያለው አንድ ብሮሹር ቅዱስ ጽሑፋዊ እውነቶችን በሚገባ ሊያስጨብጥ እንዲሁም ከአምላክ እውቀት ጋር የሚጋጩ ሐሳቦችንና ትምህርቶችን ሊያፈርስ ይችላል። — 2 ቆሮንቶስ 10:5
2 እንደ አንድ አካል ሆነው በዓለም ዙሪያ የአምላክን ፈቃድ የሚያደርጉት የይሖዋ ምሥክሮች የተባለውን ብሮሹር ካነበበ በኋላ አንድ ሰው እንዲህ ብሎ ለመጻፍ ተገፋፍቷል:- “እንዲህ ዓይነት ድርጅት በፍጹም አይቼ አላውቅም። . . . ሃይማኖታዊ ግብዝነት በበዛበት በዚህ ዘመን ውስጥ የአምላክን ፈቃድ በቁምነገር የሚይዙ ሰዎች ማግኘት በጣም የሚያስገርም ነው።” አንድ በአፍሪካ ውስጥ የሚገኝ ጠንቋይ በምድር ላይ ለዘላለም በደስታ ኑር! የተባለውን ብሮሹር አጠና። ይህ ብሮሹር በዚህ ሰው ላይ ምን ውጤት አስከተለ? የጥንቆላ ተግባሩን ተወ፤ እንዲሁም ከመጀመሪያ ሚስቱ በስተቀር አብረውት የሚኖሩትን ሌሎች ሴቶች አሰናበታቸው። ከዚያም የመጀመሪያ ሚስቱን በሕግ አገባት።
3 በሥላሴ ማመን ይኖርብሃልን? የተባለው ብሮሹር በማስረጃ የተደገፈ፣ ምክንያታዊና ውጤታማ የሆነ ለእውነት የቆመ መሣሪያ ነው። በጃማይካ ዌስት ኢንዲስ ለሚታተመው ዘ ሰንዴይ ግሊነር ለተባለው ጋዜጣ ሃይማኖት ነክ ጉዳዮችን የሚጽፉ አንድ ሰው ስለዚህ ብሮሹር አስተያየታቸውን ሲሰጡ እንዲህ ብለዋል:- “ጽሑፉ የምሥክሮቹ ድንቅ ሥራ ነው። አሁን የሥላሴም ሆነ የሁለት አምላክ አማኝ አደጋ ላይ ወድቋል። ቡክሌቱ የሥላሴ ትምህርት ከመጽሐፍ ቅዱስ የተገኘ አለመሆኑን ለማሳየት ከታሪካዊና ከቲኦሎጂያዊ ምንጮች በመጥቀስ ብዙ ማስረጃዎችን ያቀርባል። . . . ኢየሱስ እግዚአብሔር ነው የሚለውን አመለካከት በመቃወም በምሥክሮቹ የተዘጋጁትን አሳማኝና ከበድ ያሉ የመከራከሪያ ነጥቦች መጠነኛ የቤተ ክርስቲያን እውቀት ያላቸው ቀርቶ ጥሩ እውቀት አለን የሚሉትም እንኳን ይቋቋሙታል ብሎ ማሰቡ ለዚህ የሃይማኖት ነክ ጉዳዮች ጸሐፊ አስቸጋሪ ነው።”
4 በሚገባ ተጠቀሙባቸው፦ ውጤታማ ለመሆን ከተፈለገ እነዚህ ማራኪና እውቀት ሰጪ የሆኑ መሣሪያዎች ለሚያነቧቸው ሰዎች መበርከት አለባቸው። የተለያዩ ሐሳቦችን የያዙ ልዩ ልዩ ብሮሹሮች ስላሉን ለምንመሰክርለት ግለሰብ ተስማሚ ነው ብለን የምናስበውን ብሮሹር ለማበርከት ጥረት ማድረግ ይኖርብናል። የብሮሹሮቻችንን ይዘት ጥሩ አድርጎ ማወቅና የተለያዩ ብሮሹሮችን በቅርብ መያዝ በመስክ አገልግሎት፣ በቤት ወይም በማንኛውም ቦታ በሚገባ እንድንጠቀምባቸው ያስችለናል።
5 ለምሳሌ ያህል በሕዝበ ክርስትና የሥላሴ ትምህርት ግራ የተጋባ ወይም ኢየሱስ እግዚአብሔር ነው ብሎ የሚያስብ ሰው ስታነጋግሩ በየትኛው ብሮሹር ትጠቀማላችሁ? አፍቃሪ የሆነ አምላክ ይህን ሁሉ መከራ ለምን ይፈቅዳል ብሎ ለሚጠይቅ ሰው የሚያስፈልገው የትኛው ብሮሹር ነው? ሰዎችን የሚጠቅም መንግሥት ማስፈለጉ እንደሚያሳስበው ለሚገልጽልህ ሰው ተስማሚ ሊሆን የሚችለው ብሮሹር የትኛው ነው?
6 የትኛውን ብሮሹር እንደምንጠቀም ከማወቅ በተጨማሪ ብሮሹሩ ስለያዛቸው ሐሳቦች በመጥቀስ የሰውየውን ፍላጎት ለመቀስቀስ መጣር አለብን። ሁኔታዎቹ ከፈቀዱልህ ትምህርቱን እንዲያነበው የሰውየውን ፍላጎት ሊቀሰቅስ የሚችል ሐሳብ ወይም ሥዕላዊ መግለጫ አሳየው አለዚያም አንድ ወይም ሁለት አንቀጾችን አብረኸው አንብበህ የተጠቀሱትን ጥቅሶች አውጣና ተወያይበት። በዚህ መንገድ ግሩም የሆኑ ብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶች ተጀምረዋል።
7 ብሮሹሮቻችን ቅዱስ ጽሑፋዊ የሆኑ መልሶችን ይሰጣሉ፤ እንዲሁም በዓለም ውስጥ በሚሠሩት አስጸያፊ ነገሮች ለሚያዝኑና ለሚተክዙ ሰዎች ተስፋ ያዘሉ ናቸው። (ከሕዝቅኤል 9:4 ጋር አወዳድር) በግ መሰል የሆኑት ሰዎች እነዚህ ጽሑፎች የያዟቸውን መልዕክቶች ይቀበላሉ። ፍላጎት ያላቸውን ሰዎች ስንፈልግ በሁሉም ዓይነት የአገልግሎታችን ዘርፎች በብሮሹሮች በጥሩ ሁኔታ እንጠቀም።
-
-
በመጠበቂያ ግንብ እና በንቁ! መጽሔቶች በጥሩ ሁኔታ መጠቀምየመንግሥት አገልግሎት—1993 | ሐምሌ
-
-
በመጠበቂያ ግንብ እና በንቁ! መጽሔቶች በጥሩ ሁኔታ መጠቀም
1 መጠበቂያ ግንብ እና ንቁ! ዛሬ ሰዎች ከሚያነቧቸው መጽሔቶች ሁሉ የላቀ ጥቅም ያላቸው መጽሔቶች ናቸው። ለምን? ምክንያቱም የያዟቸው መንፈሳዊ እውነቶች በሰዎች ሕይወት ላይ ዘላለማዊ የሆነ መልካም ውጤት ሊኖራቸው ይችላል። ሆኖም ብዙዎች ለሚያስፈልጓቸው መንፈሳዊ ነገሮች ሙሉ በሙሉ ንቁዎች አይደሉም፤ ወይም ደግሞ ይህን መንፈሳዊ ፍላጎታቸውን እንዴት ሊያረኩት እንደሚችሉ አያውቁም። ሰዎች መንፈሳዊ ዓይናቸው እንዲከፈት በመርዳት ጳውሎስን ልንመስለው እንችላለን። — ማቴዎስ 5:3፤ ሥራ 26:18
2 ይሆናል የሚል አመለካከት ያላችሁና በሚገባ የተዘጋጃችሁ ሁኑ፦ በክልላችሁ ውስጥ እውነትን የሚቀበሉ በግ መሰል ሰዎች አይጠፉም። አንዳንዶቹ የሚያስፈልጋቸው መጽሔቶቹን እንዲያነቡ በደግነት ማበረታታት ብቻ ሊሆን ይችላል። ስለዚህ መጠበቂያ ግንብ እና ንቁ! መጽሔቶችን ስታበረክቱ ይሆናል የሚል አመለካከት ያላችሁና ተግባቢዎች ሁኑ። ሌሎች ጽሑፎችን በምታበረክቱበት ጊዜም ቢሆን መጽሔቶቹን በርከት አድርጋችሁ በመያዝ ማንኛውንም አጋጣሚ ለማበርከት ተጠቀሙበት።
3 መጽሔቶችን በማበርከት ረገድ ይበልጥ ውጤታማ ሊያደርገን የሚችለው ምንድን ነው? በመጀመሪያ ደረጃ እኛ ራሳችን የመጽሔቶቹን ጠቃሚነት በትክክል መገንዘብ አለብን። በምናበረክታቸው መጽሔቶች ውስጥ ያሉትን ትምህርቶች በደንብ ማወቅ ይኖርብናል፤ ይህም መጽሔቶቹን ለማበርከት ያለንን ትምክህትና ጉጉት ከፍ ያደርገዋል። ለመጀመሪያ ጊዜ መጽሔቶቹን ስታነቡ ይህን ሐሳብ በአእምሮአችሁ ያዙ። በአገልግሎታችሁ የምትጠቀሙባቸውን ዋና ዋና ነጥቦች ለመምረጥ ንቁዎች ሁኑ። እንዲህ እያላችሁ ራሳችሁን ጠይቁ:- ‘ይህ ትምህርት በተለይ ለእነማን ይስማማል? ይህ የሚስማማው ለቤት እመቤት ነው፣ ለወጣት ነው፣ ወይስ ለነጋዴ ነው? ይህ ነጥብ ለተማሪ፣ ላገባ ሰው፣ ስለ አካባቢው ሁኔታ ለሚጨነቅ ሰው ይስማማልን? ይበልጥ ውጤታማ ለመሆን መጽሔቶቹ ከያዟቸው ወቅታዊ ርዕሰ ትምህርቶች በግል ያገኘነውን እውቀትና ጥቅም መሠረት አድርገን መጽሔቶቹን እንዲያነቡ ለማበረታታት መቻል ይኖርብናል።
4 የቆዩ እትሞችን በሚገባ ተጠቀሙባቸው፦ መጠበቂያ ግንብ እና ንቁ! መጽሔቶች ከታተሙበት ቀን በአንድ ወይም በሁለት ወር ውስጥ ሁሉም መበርከት ባይችሉም እንኳን ያላቸውን ጠቃሚነት እንደማያጡ አስታውሱ። የያዟቸውን ሐሳቦች ጊዜ አይሽራቸውም፤ በጥሩ ሁኔታ አስቀምጠናቸው ከሆነ የቆዩትን ቅጂዎችም ቢሆን ከማበርከት ወደኋላ ማለት የለብንም። የቆዩ መጽሔቶች እንዲከማቹ ማድረግና በፍጹም አለመጠቀም ለእነዚህ ጠቃሚ መሣሪያዎች አድናቆት እንደጎደለን ያሳያል። እያንዳንዱ መጽሔት መንፈሳዊ ፍላጎቶችን የሚቀሰቅሱና የሚያረኩ እውነቶችን ይዟል። የቆዩትን እትሞች ከማስቀመጥና ከመርሳት ይልቅ እነዚህን መጽሔቶች ፍላጎት ላላቸው ሰዎች ለማበርከት ልዩ ጥረት ማድረግ አይሻልምን?
5 የንቁ! መጽሔት በመጀመሪያ ጊዜ መንፈሳዊ ዝንባሌ ያልነበራቸው ብዙ ሰዎች ለመንፈሳዊ ፍላጎታቸው ንቁዎች እንዲሆኑ ረድቷቸዋል። የይሖዋን ሕዝብ በመንፈሳዊ ለመመገብ በወጣው ፕሮግራም ውስጥ መጠበቂያ ግንብ ዋነኛ መሣሪያ ነው። እነዚህ መጽሔቶች በግሩም ሁኔታ እርስ በርስ ይደጋገፋሉ፤ የምሥራቹም እንዲሰበክ ከፍተኛ ሚና ይጫወታሉ።
6 ማንኛውንም አጋጣሚ መጽሔቶችን ለማበርከት ከተጠቀምንበት እነዚህ መጽሔቶች በግ መሰል የሆኑትን ሰዎች መንፈሳዊ ፍላጎት ውጤታማ በሆነ መንገድ ሊያረኩ እንደሚችሉ ሙሉ በሙሉ ትምክህት ሊኖረን ይችላል። ይሆናል የሚል አመለካከት ለመያዝ፣ በሚገባ ለመዘጋጀትና በአገልግሎቱ አዘውታሪዎች ለመሆን እንፈልጋለን። የምሥራቹ አስፋፊዎች እንደመሆናችን መጠን ሁላችንም በመጠበቂያ ግንብ እና በንቁ መጽሔቶች አዘውትረን በጥሩ ሁኔታ እንጠቀምባቸው።
-