-
አንድ ክርስቲያን ከቀብር ሥነ ሥርዓት ጋር ለተያያዙ ልማዶች የሚኖረው አመለካከትመጠበቂያ ግንብ—1998 | ሐምሌ 15
-
-
ላይ ለመገኘት ይስማሙ ይሆናል። ይሁን እንጂ አንዳንዶቹ አምባጓሮ ቢያስነሱስ? በዚህ ጊዜም ጉዳዩን ለማስረዳት መሞከሩ ጠብ ከመፍጠር በቀር ምንም የሚፈይደው ነገር አይኖር ይሆናል። ‘የጌታም ባሪያ ትዕግሥተኛ ሊሆን እንጂ ሊጣላ አይገባውም።’ (2 ጢሞቴዎስ 2:24) ስለዚህ ለመተባበር አሻፈረኝ ያሉት ዘመዶች በኃይል ለመጠቀም ሲሞክሩ ባሏን በሞት ያጣችው ክርስቲያን ሴትና ልጆቿ ሁኔታው ከቁጥጥራቸው ውጪ ሊሆን ይችላል። ይሁን እንጂ “ከማያምኑ ጋር በማይመች አካሄድ አትጠመዱ” የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ትእዛዝ በጥብቅ ስለሚከተሉ በቤታቸው ውስጥ በሚከናወነው የሐሰት ሃይማኖት ሥነ ሥርዓት ላይ ተካፋይ አይሆኑም።—2 ቆሮንቶስ 6:14
ይህ መሠረታዊ ሥርዓት የቀብር ሥነ ሥርዓት በሚፈጸምበትም ጊዜ ይሠራል። የይሖዋ ምሥክሮች በአንድ የሐሰት ሃይማኖት አገልጋይ አማካኝነት በሚካሄድ መዝሙር፣ ጸሎትና ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓት ተካፋይ አይሆኑም። ከቤተሰቡ አባላት ጋር የቀረበ ዝምድና ያላቸው ክርስቲያኖች እንዲህ በመሰለው ሥነ ሥርዓት ላይ መገኘት እንዳለባቸው ተሰምቷቸው ቢገኙ እንኳ በእነዚህ ነገሮች አይካፈሉም።—2 ቆሮንቶስ 6:17፤ ራእይ 18:4
ክብር ባለው መንገድ የሚፈጸም የቀብር ሥነ ሥርዓት
የይሖዋ ምሥክሮች በሚያካሂዱት የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ሟቹን ላለማስቆጣት ሲባል የሚፈጸም ምንም ዓይነት ሃይማኖታዊ ሥርዓት የለም። በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተመሠረተ ንግግር በመንግሥት አዳራሹ ወይም በሟቹ ቤት አለዚያም ደግሞ በመቃብሩ ቦታ ይሰጣል። የንግግሩ ዓላማ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ሙታንና ስለ ትንሣኤ ተስፋ ምን እንደሚል በማብራራት ሐዘን ላይ የሚገኙትን ሰዎች ማጽናናት ነው። (ዮሐንስ 11:25፤ ሮሜ 5:12፤ 2 ጴጥሮስ 3:13) በቅዱሳን ጽሑፎች ላይ የተመሠረተ መዝሙር ሊዘመር ይችላል፤ ከዚያም ሥርዓቱ በሚያጽናና ጸሎት ይደመደማል።
በቅርቡ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት የኔልሰን ማንዴላ ታናሽ እህት የሆኑ አንዲት የይሖዋ ምሥክር በሞቱ ጊዜ እንዲህ የመሰለው የቀብር ሥነ ሥርዓት ተፈጽሞ ነበር። ሥነ ሥርዓቱ ከተፈጸመ በኋላ ፕሬዚዳንቱ ተናጋሪውን ከልባቸው አመስግነውታል። በርካታ ሹማምንቶችና ከፍተኛ የመንግሥት ባለ ሥልጣናት በቦታው ተገኝተው ነበር። አንዲት የካቢኔ ሚኒስትር “እስካሁን ከተገኘሁባቸው የቀብር ሥነ ሥርዓቶች ሁሉ ይበልጥ ክብር የተላበሰ ነበር” በማለት ተናግረዋል።
የሐዘን ልብሶች መልበስ ተገቢ ነው?
የይሖዋ ምሥክሮች የሚወዱትን ሰው በሞት ሲያጡ ጥልቅ ሐዘን ያድርባቸዋል። ልክ እንደ ኢየሱስ እንባቸውን ያፈስሳሉ። (ዮሐንስ 11:35, 36) ይሁን እንጂ የደረሰባቸውን ሐዘን ውጫዊ በሆነ መግለጫ ለሕዝብ ማሳወቁ አስፈላጊ ሆኖ አይታያቸውም። (ከማቴዎስ 6:16-18 ጋር አወዳድር።) በብዙ አገሮች ባል የሞተባቸው ሴቶች ሟቹን ላለማስቆጣት ሲባል የተለየ የሐዘን ልብስ እንዲለብሱ ይጠበቅባቸዋል። እነዚህ ልብሶች ሟቹ ከተቀበረ በኋላ ለበርካታ ወራት ወይም ለአንድ ዓመት ያህል መለበስ አለባቸው። ልብሶቹን መልበሳቸውን የሚያቆሙት ሌላ ድግስ በሚደገስበት ጊዜ ነው።
የሐዘን ምልክት የሆነውን ይህን ልብስ አለመልበስ ሟቹን ሰው እንደ ማስቀየም ተደርጎ ይቆጠራል። በዚህ ምክንያት በስዋዚላንድ የሚገኙ አንዳንድ የጎሳ አለቆች የይሖዋ ምሥክሮችን ከገዛ ቤታቸውና ከቄያቸው አባርረዋቸዋል። ሆኖም እነዚህ ታማኝ ክርስቲያኖች በሌላ ቦታ በሚኖሩ መንፈሳዊ ወንድሞቻቸው አስፈላጊው እንክብካቤ ተደርጎላቸዋል።
የስዋዚላንድ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የተባረሩት የይሖዋ ምሥክሮች ወደ ቤታቸውና ወደ መንደራቸው መመለስ እንዲችሉ ፈርዶላቸዋል። በሌላ በኩል ደግሞ ባሏ የሞተባት አንዲት ክርስቲያን ሴት የሞተው ባሏ የሐዘን ልብስ መልበስ እንደሌለባት የገለጸበትን ደብዳቤና የቴፕ ክር ካቀረበች በኋላ ከቤቷ ሳትፈናቀል እንድትኖር ተፈቅዶላታል። በዚህ መንገድ ለባሏ አክብሮት ያላት መሆኑን ማሳየት ችላለች።
አንድ ሰው በተለይ ቅዱስ ጽሑፋዊ ያልሆኑ ልማዶች በሚዘወተሩበት አካባቢ የሚኖር ከሆነ ከመሞቱ በፊት የቀብር ሥነ ሥርዓቱ እንዴት መከናወን እንዳለበት የሚገልጽ ግልጽ መመሪያ መስጠቱ ትልቅ ጥቅም አለው። ቪክቶር የተባለውን ካሜሩናዊ ምሳሌ ተመልከት። የቀብር ሥነ ሥርዓቱ የሚፈጸምበትን መንገድ ግልጽ አድርጎ በጽሑፍ አሰፈረ። የሰውን ራስ ቅል ማምለክን ጨምሮ ከሙታን ጋር በተያያዘ የተለያዩ ልማዶችን አጥብቀው የሚከተሉ ተደማጭነት ያላቸው በርካታ ዘመዶች ነበሩት። ቪክቶር በዘመዶቹ የተከበረ ሰው እንደመሆኑ መጠን የእሱንም የራስ ቅል ለዚህ ዓላማ ሊያውሉት እንደሚችሉ ተገነዘበ። በዚህም የተነሳ የይሖዋ ምሥክሮች የእርሱን የቀብር ሥነ ሥርዓት እንዴት ሊያከናውኑ እንደሚገባ የሚገልጽ ግልጽ የሆነ መመሪያ አዘጋጀ። ይህም ለሚስቱና ለልጆቹ ሁኔታውን አቀለለላቸው። ለማኅበረሰቡም ጥሩ ምሥክርነት ሊሰጥ ችሏል።
ቅዱስ ጽሑፋዊ ያልሆኑ ልማዶችን ከመከተል ራቁ
የመጽሐፍ ቅዱስ እውቀት ያላቸው አንዳንድ ሰዎች ከሌሎች ሰዎች የተለዩ ሆነው መታየት ይፈራሉ። ስደት እንዳይደርስባቸው ሲሉ ሌሊቱን ሙሉ አስከሬን ሲጠብቁ የማደርን ልማድ የሚከተሉ መስለው በመታየት ጎረቤቶቻቸውን ለማስደሰት ይጥራሉ። በግል ማጽናኛ ለመስጠት ተብሎ በሐዘን ላይ የሚገኙ ሰዎችን መጠየቁ የሚያስመሰግን ቢሆንም አስከሬኑ ከመቀበሩ በፊት ባሉት ቀናት ሌሊት ሌሊት በሟቹ ቤት ከቀብር ጋር የተያያዘ ልዩ ሥርዓት ማከናወን ተገቢ አይደለም። እንዲህ ማድረጉ ሌሎች ተመልካቾች መጽሐፍ ቅዱስ ሙታን ስላሉበት ሁኔታ የሚናገረውን ነገር አያምኑበትም የሚል ስሜት አድሮባቸው እንዲደናቀፉ ሊያደርግ ይችላል።—1 ቆሮንቶስ 10:32
መጽሐፍ ቅዱስ ክርስቲያኖች ለአምላክ የሚያቀርቡትን አምልኮ በሕይወታቸው ውስጥ ቅድሚያ እንዲሰጡትና ጊዜያቸውን በጥበብ እንዲጠቀሙበት አጥብቆ ያሳስባቸዋል። (ማቴዎስ 6:33፤ ኤፌሶን 5:15, 16) ሆኖም በአንዳንድ ቦታዎች በቀብር ሥነ ሥርዓት ምክንያት የጉባኤ እንቅስቃሴዎች ለአንድ ሳምንት ወይም ከዚያ ለሚበልጥ ጊዜ ይቋረጣሉ። ይህ በአፍሪካ ብቻ ያለ ችግር አይደለም። አንድን የቀብር ሥነ ሥርዓት በማስመልከት ከደቡብ አሜሪካ የተላከ አንድ ሪፖርት እንዲህ ይላል:- “ሦስት ክርስቲያናዊ ስብሰባዎች የነበራቸው የተሰብሳቢ ቁጥር በጣም አነስተኛ ነበር። የመስክ አገልግሎት ለአሥር ቀናት ገደማ ተቋርጦ ነበር። የይሖዋ ምሥክሮች ያልሆኑ ሰዎችና የመጽሐፍ ቅዱስ ተማሪዎች እንኳ አንዳንድ ወንድሞችና እህቶች በአንዳንድ ሥርዓቶች ላይ ያደርጉት በነበረው ተሳትፎ ከመገረማቸውም በላይ ቅር ተሰኝተዋል።”
በአንዳንድ ማኅበረሰቦች ሐዘን የደረሰበት ቤተሰብ የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ከተፈጸመ በኋላ የቅርብ ወዳጆችን በመጥራት ቀለል ያለ ምግብ ይጋብዛል። ይሁን እንጂ በብዙ የአፍሪካ አገሮች በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙ በመቶ የሚቆጠሩ ሰዎች ብዙውን ጊዜ ከብት በሚታረድበት ድል ያለ ድግስ ላይ ለመገኘት ወደ ሟቹ ቤት ይጎርፋሉ። በክርስቲያን ጉባኤ ውስጥ ያሉ አንዳንዶች ይህንኑ ልማድ ኮርጀዋል፤ እንዲህ ማድረጋቸው ደግሞ ሟቹን ላለማስቆጣት ሲባል በሚደገሱት ልማዳዊ ድግሶች ያምናሉ የሚል አመለካከት በሌሎች ዘንድ አሳድሯል።
የይሖዋ ምሥክሮች የሚያከናውኑት የቀብር ሥነ ሥርዓት ሐዘን በደረሰባቸው ሰዎች ላይ ተጨማሪ ሸክም የሚጭን አይደለም። ስለዚህ ለተንዛዛ የቀብር ሥነ ሥርዓት የሚወጣውን ወጪ ለመሸፈን ለቅሶ ከሚደርሱ ሰዎች ገንዘብ መሰብሰብ አግባብ አይደለም። በሐዘን ላይ የወደቁ ድሃ መበለቶች የሚያስፈልጋቸውን ወጪ ለመሸፈን የሚያስችል አቅም በማይኖራቸው ጊዜ በጉባኤ ያሉት ሌሎች ድጋፍ ለመስጠት ፈቃደኞች እንደሚሆኑ ጥርጥር የለውም። በዚህ መንገድ የሚደረገው እርዳታ በቂ ካልሆነ ሽማግሌዎች ችግር ላይ ለወደቁት ቁሳዊ ድጋፍ ለመስጠት ዝግጅት ሊያደርጉ ይችላሉ።—1 ጢሞቴዎስ 5:3, 4
ሁሉም የቀብር ሥነ ሥርዓቶች ከመጽሐፍ ቅዱስ መሠረታዊ ሥርዓቶች ጋር ይጋጫሉ ማለት አይደለም። ሆኖም ከመጽሐፍ ቅዱስ መሠረታዊ ሥርዓቶች ጋር በሚጋጩበት ጊዜ ክርስቲያኖች ቅዱሳን ጽሑፎች ከሚሉት ጋር ተስማምተው ለመሄድ ቁርጥ ውሳኔ ያደርጋሉ።c (ሥራ 5:29) እንዲህ ማድረጉ ተጨማሪ መከራ ሊያስከትል ቢችልም ብዙ የአምላክ አገልጋዮች እንዲህ ያሉትን ፈተናዎች በተሳካ ሁኔታ መወጣት ችለዋል። “የመጽናናትም ሁሉ አምላክ” ከሆነው ከይሖዋ ባገኙት ብርታትና በመከራቸው ባጽናኗቸው የእምነት ባልደረቦቻቸው ባገኙት ፍቅራዊ እርዳታ ፈተናዎቹን በድል አድራጊነት ተወጥተዋል።—2 ቆሮንቶስ 1:3, 4
-
-
ጥቅምት 3, 1998 የሚደረገው ዓመታዊ ስብሰባመጠበቂያ ግንብ—1998 | ሐምሌ 15
-
-
ጥቅምት 3, 1998 የሚደረገው ዓመታዊ ስብሰባ
የፔንሲልቬንያ የመጠበቂያ ግንብ የመጽሐፍ ቅዱስና ትራክት ማኅበር አባላት ዓመታዊ ስብሰባ ጥቅምት 3, 1998 በኒው ጀርሲ ክፍለ ሀገር፣ በጀርሲ ከተማ 2932 ኬኔዲ በሊቨርድ በሚገኘው የይሖዋ ምሥክሮች መሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል። አባላቱ ብቻ የሚገኙበት ስብሰባ ከጠዋቱ 3:15 ከተደረገ በኋላ 4 ሰዓት ላይ አጠቃላይ ዓመታዊው ስብሰባ ይደረጋል።
ካለፈው ዓመት ወዲህ የፖስታ አድራሻቸውን የለወጡ የማኅበሩ አባላት መደበኛዎቹ የማስታወቂያ ደብዳቤዎችና የውክልና ማስረጃዎች በሐምሌ ወር ውስጥ እንዲደርሷቸው ለውጡን አሁኑኑ ለጸሐፊው ቢሮ ማስታወቅ ይኖርባቸዋል።
ከዓመታዊው የስብሰባ ማስታወቂያዎች ጋር ለአባላቱ የሚላኩት ውክልናዎች ከነሐሴ 1 በፊት ለማኅበሩ ጽሕፈት ቤት ተመልሰው መድረስ አለባቸው። እያንዳንዱ አባል በስብሰባው ላይ ራሱ ይገኝ ወይም አይገኝ እንደሆነ በመግለጽ ውክልናውን ወዲያውኑ ሞልቶ መመለስ አለበት። በስብሰባው ላይ ማን እንደሚገኝ የሚታወቀው በዚህ መሠረት ስለሆነ በእያንዳንዱ የውክልና ቅጽ ላይ የሚሰጠው መረጃ በዚህ ነጥብ ላይ ግልጽ መሆን ይኖርበታል።
መደበኛውን የሥራ ጉዳይና ሪፖርት ጨምሮ ጠቅላላው ስብሰባ ከቀኑ 7 ሰዓት ወይም ከዚያ ብዙ ሳይቆይ ያበቃል ተብሎ ይጠበቃል። ከሰዓት በኋላ ስብሰባ አይኖርም። ያለው ቦታ የተወሰነ በመሆኑ መግባት የሚቻለው በቲኬት ብቻ ይሆናል። ዓመታዊውን ስብሰባ ወደ ሌሎች አዳራሾች በስልክ ለማስተላለፍ የተደረገ ዝግጅት የለም።
-