-
ይሖዋከቅዱሳን ጽሑፎች እየጠቀሱ ማመራመር
-
-
መጽሐፍ ቅዱስ ይሖዋን መውደድና (ሉቃስ 10:27) መፍራት እንዳለብን ይናገራል። (1 ጴጥ. 2:17፤ ምሳሌ 1:7፤ 2:1–5፤ 16:6) ለአምላክ ያለን ጤናማ ፍርሃት እርሱን የሚያስከፋውን ከማድረግ እንድንጠነቀቅ ያደርገናል። ለይሖዋ ያለን ፍቅር እርሱን የሚያስደስቱትን ነገሮች ለመሥራትና ከመጠን በላይ ለሆነ ፍቅሩና የማይገባ ደግነቱ አድናቆታችንን እንድንገልጽ ይገፋፋናል።
ምሳሌ:- አንድ ልጅ አባቱን ላለማስከፋት ይፈራል። ይህ ተገቢ ቢሆንም አባቱ ላደረገለት ነገር ያለው አድናቆት እውነተኛ ፍቅሩንም እንዲገልጽለት ሊገፋፋው ይገባል። ውኃ ውስጥ ጠልቆ የሚዋኝ አንድ ዋናተኛ ባሕር እወዳለሁ ሊል ይችላል። ሆኖም ያለው ጤናማ ፍርሃት ሊጠነቀቅባቸው የሚገቡ አንዳንድ ነገሮችም እንዳሉ እንዲያውቅ ያደርገዋል። በተመሳሳይ ለአምላክ ያለን ፍቅር እርሱን የማያስደስት ነገር እንዳንሠራ ከምናሳየው ጤናማ ፍርሃት ጋር አብሮ የሚሄድ መሆን ይኖርበታል።
-
-
የይሖዋ ምሥክሮችከቅዱሳን ጽሑፎች እየጠቀሱ ማመራመር
-
-
የይሖዋ ምሥክሮች
ፍቺ:- ስለ ይሖዋ አምላክና እርሱ ለሰው ልጆች ስላለው ዓላማዎች በትጋት ምሥክርነት የሚሰጡ ሰዎች የሚገኙበት ዓለም አቀፍ ክርስቲያናዊ ማኅበረሰብ ናቸው። የእምነታቸው መሠረት የሚያደርጉት መጽሐፍ ቅዱስን ብቻ ነው።
የይሖዋ ምሥክሮችን ከሌሎች ሃይማኖቶች የተለዩ የሚያደርጓቸው እምነቶች ምንድን ናቸው?
(1) መጽሐፍ ቅዱስ:- የይሖዋ ምሥክሮች ጠቅላላው መጽሐፍ ቅዱስ በአምላክ መንፈስ አነሣሽነት የተጻፈ የአምላክ ቃል ነው ብለው ያምናሉ፤
-