-
መጽሐፍ ቅዱስን በሚገባ ተጠቀሙበትየመንግሥት አገልግሎት—2004 | መስከረም
-
-
መጽሐፍ ቅዱስን በሚገባ ተጠቀሙበት
1 በአገልግሎት ላይ ልናበረክተው ያሰብነው የትኛውንም ጽሑፍ ቢሆን ለመስማት ፈቃደኛ ለሆኑ ሰዎች ልናነብ የምንችለው ትኩረታቸውን የሚስብ ጥቅስ ማዘጋጀታችን ጠቃሚ ነው። (ዕብ. 4:12) በምታበረክተው ጽሑፍ ላይ የሚገኝ ጥቅስ መርጠህ ከመጽሐፍ ቅዱስ ማንበብህ ጽሑፉን ለማስተዋወቅ ቀላል ያደርግልሃል። በአንዳንድ አካባቢዎች አስፋፊዎች በመንገድ ላይ ወይም ከቤት ወደ ቤት ሲያገለግሉ መጽሐፍ ቅዱሳቸውን በእጃቸው መያዙን ጠቃሚ ሆኖ አግኝተውታል።
2 ውይይቱን በጥቅስ ጀምር፦ አንዳንድ አስፋፊዎች ቀጥለው ሊያነቡት ባሰቡት ጥቅስ ላይ የተመሠረተ ቀለል ያለ የአመለካከት ጥያቄ ለሚያነጋግሩት ሰው በማቅረብ ውይይቱን ይጀምራሉ። እንዲህ ማድረጉ የሰውየውን ትኩረት ወዲያውኑ ወደ አምላክ ቃል ለማዞር ይረዳል። ከዚህ ቀጥሎ የቀረቡትን የመግቢያ ሐሳቦች አንተ ባለህበት ክልል ውስጥ ልትጠቀምባቸው ትችል ይሆን?
◼ “ኃይል ቢኖርዎት ኖሮ በዚህ ጥቅስ ላይ የተገለጹትን ለውጦች ያመጡ ነበር?” ራእይ 21:4ን አንብብ።
◼ “የምንኖርበት ዘመን ይህን ያህል አስጨናቂ የሆነው ለምንድን ነው?” 2 ጢሞቴዎስ 3:1-5ን አንብብ።
◼ “ሁሉም ሰው በዚህ ጥቅስ ላይ የሚገኘውን ምክር ተግባራዊ ቢያደርግ የተሻለ ኅብረተሰብ የሚኖር ይመስልዎታል?” ማቴዎስ 7:12ን አንብብ።
◼ “ልጆችዎ በዚህ ጥቅስ ላይ የሰፈረው ሁኔታ ሲፈጸም መመልከት የሚችሉ ይመስልዎታል?” መዝሙር 37:10, 11ን አንብብ።
◼ “እነዚህ ቃላት የሚፈጸሙበት ጊዜ ይመጣል ብለው ያስባሉ?” ኢሳይያስ 33:24ን አንብብ።
◼ “በዚህ ጥቅስ ላይ ስለተገለጸው የመንግሥት ለውጥ ከዚህ በፊት ሰምተው ያውቃሉ?” ዳንኤል 2:44ን አንብብ።
◼ “አምላክን እንደሚከተለው ብለው ለመጠየቅ አስበው ያውቃሉ?” ኢዮብ 21:7ን አንብብ።
◼ “በሞት የተለዩንን የምንወዳቸው ሰዎች እንደገና ማግኘት የምንችል ይመስልዎታል?” ዮሐንስ 5:28, 29ን አንብብ።
◼ “የሞቱ ሰዎች ስለ እኛ ማወቅ ይችላሉ?” መክብብ 9:5ን አንብብ።
3 ጥቅሱን ማብራራት፣ በምሳሌ ማስረዳትና ከምታወያየው ነጥብ ጋር ማዛመድ፦ ለመወያየት ፈቃደኛ የሆነ ሰው ስታገኝ ውይይቱን በአጭሩ ከመቋጨት ይልቅ ጊዜ ወስደህ ያነበብክለትን ጥቅስ በማብራራት፣ በምሳሌ በማስረዳትና ከምትወያዩበት ነጥብ ጋር በማዛመድ ይበልጥ ግልጽ እንዲሆንለት እርዳው። (ነህ. 8:8) ሰዎች በአምላክ ቃል ውስጥ የሚገኘውን ትምህርት ሲረዱትና ሲቀበሉት በሕይወታቸው ውስጥ አስደናቂ ለውጦች እንዲያደርጉ ያነሳሳቸዋል።—1 ተሰ. 2:13
4 የግለሰቡን ፍላጎት ለማሳደግ እየጣርክ በመጽሐፍ ቅዱስ በሚገባ መጠቀምህን ቀጥል። ተመላልሶ መጠየቅ ስታደርግም ከላይ በተገለጸው መንገድ መጠቀም ትችላለህ። ይኸውም (1) ተስማሚ የሆነ ጥቅስ ምረጥ። (2) ጥቅሱን በተመለከተ ቀለል ያለ የአመለካከት ጥያቄ ካቀረብህለት በኋላ ጥቅሱን አንብበው። (3) ጥቅሱን በማብራራት፣ በምሳሌ በማስረዳትና ከምትወያዩበት ጉዳይ ጋር በማዛመድ ነጥቡ እንዲገባው አድርግ። ተመላልሶ መጠየቅ ባደረግህለት ቁጥር ግለሰቡ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ያለውን እውቀት ለማሳደግ ጥረት አድርግ። ብዙም ሳይቆይ ጥናት ልታስጀምረው ትችል ይሆናል!
-
-
መጽሔቶችን ለማበርከት ምን ማለት ይቻላል?የመንግሥት አገልግሎት—2004 | መስከረም
-
-
መጽሔቶችን ለማበርከት ምን ማለት ይቻላል?
መጠበቂያ ግንብ ሐምሌ 1
“ብዙዎች ችግር ሲያጋጥማቸው ‘አምላክ በእርግጥ ለሰዎች ያስባል? የሚደርስብንን መከራስ ይመለከታል?’ የሚል ጥያቄ ያነሳሉ። እርስዎስ ስለዚህ ጉዳይ አስበው ያውቃሉ? [መልስ እንዲሰጥ ፍቀድለት።] ይህ መጽሔት አምላክ በዛሬው ጊዜ ለእኛ እንደሚያስብልን ያሳየባቸውን መንገዶች እንዲሁም መከራን ሙሉ በሙሉ ለማስወገድ ያደረገውን ዝግጅት ይገልጻል።” ዮሐንስ 3:16ን አንብብ።
ንቁ! ሐምሌ 2004
“በዛሬው ጊዜ በርካታ ሰዎች በብቸኝነት ይሰቃያሉ። ብቸኝነት ከሌሎች ሰዎች የመነጠልና የመገለል ስሜት ያሳድራል። ይህ ስሜትን የሚጎዳ ነው ቢባል አይስማሙም? [መልስ እንዲሰጥ ፍቀድለት። ከዚያም መዝሙር 25:16ን አንብብ።] ይህ የንቁ! እትም ብቸኝነትን ለማሸነፍ የሚረዱ ጠቃሚ ምክሮችን ይዟል።”
መጠበቂያ ግንብ ሐምሌ 15
“አብዛኞቹ ሰዎች በዛሬው ጊዜ እንደዚህ ያለ ክንውን [በሽፋኑ ላይ የሚገኘውን ሥዕል አሳየው] እንደተፈጸመ የሚገልጽ ዜና ቢሰሙ ለማመን ይከብዳቸው ይሆናል። እርስዎስ ምን ይላሉ? [መልስ እንዲሰጥ ፍቀድለት። ከዚያም ማርቆስ 4:39ን አንብብ።] ኢየሱስ ፈጽሟቸዋል የሚባሉት ተዓምራት እውነተኛ ለመሆናቸው ምን ማስረጃ አለ? ይህ የመጠበቂያ ግንብ እትም ለዚህ ጥያቄ መልስ ይሰጣል።”
Awake! July 22
“በዘመናችን ወንጀለኞች ሰዎችን ለማጭበርበር በየጊዜው የተለያዩ ዘዴዎችን ይቀይሳሉ። ይህ ሁኔታ ያሳስብዎታል? [መልስ እንዲሰጥ ፍቀድለት።] ይህ የንቁ! እትም እንዳንጭበረበር ሊረዱን የሚችሉ ጥቂት መሠረታዊ ነጥቦችን ያብራራል።” ምሳሌ 22:3ን አንብብ።
-