-
ስለ መጪው ጊዜ ያለን አመለካከትትምህርት ቤትና የይሖዋ ምሥክሮች
-
-
ስለ መጪው ጊዜ ያለን አመለካከት
ለሕይወት ያለንን አመለካከት በጥልቅ የሚነካ የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢት በራእይ 21:3, 4 ላይ ይገኛል። እንዲህ ይነበባል:- “እግዚአብሔር እሱ ራሱ ከእነርሱ [ከሰዎች] ጋር ሆኖ አምላካቸው ይሆናል። እንባዎችንም ከዓይኖቻቸው ያብሳል፣ ሞትም ከእንግዲህ ወዲህ አይሆንም፣ ኀዘንም ቢሆን ወይም ጩኸት ወይም ሥቃይ ከእንግዲህ ወዲህ አይሆንም፣ የቀደመው ሥርዓት አልፎአልና።”
መጽሐፍ ቅዱስ አምላክ ስለሚፈጥረው የተሻለ ዓለም በተደጋጋሚ ይገልጻል:- “ጽድቅ የሚኖርባትን አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር እንደተስፋ ቃሉ እንጠብቃለን።”—2 ጴጥሮስ 3:13፤ መዝሙር 37:9–11, 29፤ ኢሳይያስ 11:6–9፤ 35:5, 6
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን “መንግሥትህ ትምጣ፤ ፈቃድህ በሰማይ እንደሆነች እንዲሁ በምድር ትሁን” ብለው እንዲጸልዩ ባስተማራቸው ጊዜ እንዳመለከተው የይሖዋ ምሥክሮች የሰው ልጆች ችግሮች ብቸኛ መፍትሔ የዚህ ተስፋ ፍጻሜ እንደሆነ ያምናሉ። (ማቴዎስ 6:10) የአምላክ መንግሥት እውነተኛ መስተዳድር እንደሆነች እናምናለን። (ኢሳይያስ 9:6, 7) የሰውን ልጆች የሚያስጨንቁትን ሁኔታዎች በሙሉ ከምድር ላይ አጥፍታ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የምትችል ብቸኛ መንግሥት ነች።
የአምላክ መንግሥት መምጣት በአሁኑ ጊዜ ባሉት መንግሥታት ላይ ምን ውጤት እንደሚያስከትል በሌላ የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢት ላይ ተገልጿል:- “የሰማይ አምላክ ለዘላለም የማይፈርስ መንግሥት ያስነሣል. . . እነዚያንም መንግሥታት ሁሉ ትፈጫቸዋለች። ታጠፋቸውማለች። ለዘላለምም ትቆማለች።”—ዳንኤል 2:44
ይህ ለውጥ በጣም እንደቀረበ ስለምናምን ወጣቶቻችን የአምላክ መንግሥት እውነተኛ መስተዳድር ስለመሆኗ ካለን እምነት ጋር ለሚስማማ የዕድሜ ልክ ሥራ መዘጋጀት ተገቢ መሆኑን ያምናሉ። ዋነኛ ዓላማችን በፊታችን ስላለው ብሩህ ተስፋ ለሰዎች መናገር ነው። በአሁኑ ጊዜ ያሉትን ኀዘኖችና ችግሮች አልፈን አምላክ ለሚያገለግሉት ያዘጋጃቸውን በረከቶች የምናገኝበትን ጊዜ በታላቅ ጉጉት እንጠብቃለን። እርግጠኛ የሆነው የአምላክ ተስፋ “ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ። የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል” ይላል። 1 ዮሐንስ 2:17
ከዓለም መለየት
የይሖዋ ምሥክሮች ስለ መጪው ጊዜ ያላቸው ይህ አመለካከት በመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ላይም ትልቅ ውጤት አስከትሎ እንደነበረ መገመት አያስቸግርም። ከዓለም የተለዩ ሰዎች እንዲሆኑ አድርጓቸዋል። ታሪክ ጸሐፊው ኢ ጂ ሃርዲ ክርስቲያኒቲ ኤንድ ዘ ሮማን ገቨርንመንት በተሰኘው መጽሐፋቸው ላይ እንደገለጹት “ክርስቲያኖቹ በዙሪያቸው በነበረው ዓለም እንግዶችና መጻተኞች ነበሩ። ዜግነታቸው በሰማይ ነበር። የሚጠብቋት መንግሥት የዚህ ዓለም አልነበረችም። ስለዚህ ከመጀመሪያ ጀምሮ በሕዝባዊ ጉዳዮች ውስጥ ለመግባት አለመፈለግ የክርስትና ግልጽ ገጽታ ሆነ።”
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ ተለይተው ከሚታወቁባቸው ዋነኛ ባሕርያት አንዱ ከዓለም መለየታቸው እንደሆነ ገልጿል። “ከዓለም አይደሉም” ብሏል። (ዮሐንስ 17:16፤ 15:19) የይሖዋ ምሥክሮችም ከዚህ መሠረታዊ ሥርዓት ጋር በመስማማት “የዓለም ክፍል” ላለመሆን ይጥራሉ። እርግጥ ነው፣ እንዲህ ሲባል ራሳችንን ከዓለም ሰውረን ባህታውያን እንሆናለን ማለት አይደለም። በምንኖርበት ማኅበረሰብና በትምህርት ቤት ስላሉት ሰዎች ደህንነት ከልብ እናስባለን። ወጣቶቻችንም ለትምህርት ቤት እንቅስቃሴዎች ጠቃሚ አስተዋጽኦ ለማበርከት ይፈልጋሉ።
ይሁን እንጂ ከዚህ ጋር አብረን “ዓለምም በሞላው በክፉው እንደተያዘ” መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ እንደሚናገር እናምናለን። (1 ዮሐንስ 5:19፤ ዮሐንስ 12:31፤ 2 ቆሮንቶስ 4:4) በመሆኑም የዓለም ተጽዕኖ በልጆቻችን ላይ ስለሚኖረው ጐጂ ውጤት እናስባለን። ብዙውን ጊዜ እኛ ከጥሩ ሥነ ምግባር ውጭ እንደሆነ የምናምነውን አኗኗር ዓለም አስውቦ ያቀርበዋል። ትምህርት ቤቶችም በዚህ ይነካሉ። ስለዚህ የይሖዋ ምሥክሮች በተቻለ መጠን ልጆቻቸው እነዚህን ከመሰሉት ጐጂ ተጽዕኖዎች እንዲርቁ ይፈልጋሉ።
-
-
የምንከተላቸው የሥነ ምግባር ደንቦችትምህርት ቤትና የይሖዋ ምሥክሮች
-
-
የምንከተላቸው የሥነ ምግባር ደንቦች
በሥነ ምግባር ረገድ ያለው አመለካከት በአስገራሚ ሁኔታ መለወጡ በወጣቶች ላይ መጥፎ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የይሖዋ ምሥክሮች ያምናሉ። እንደምታውቁት አዲስ ሥነ ምግባር የተባለው የሥነ ምግባር አመለካከት ከ1960ዎቹ ዓመታት ጀምሮ ተስፋፍቷል። የዚህ አዲስ ሥነ ምግባር የመጀመሪያ ደጋፊዎች ከነበሩት አንዱ እንግሊዛዊው የውልዊች ጳጳስ እንዲህ ብለዋል:- “በራሱ ‘መጥፎ’ ሊሆን የሚችል ምንም ነገር የለም።” ከዚህ አባባል ጋር አንስማማም። ይሁን እንጂ ይህን የመሰለ አመለካከት ካላቸው ጋር መከራከር እንደማንፈልግ ግልጽ ማድረግ እንፈልጋለን። ፍላጎታችን የምንከተላቸውን የሥነ ምግባር ሥርዓቶችና እነዚህን ሥርዓቶች የምንከተልባቸውን ምክንያቶች ለመግለጽ ነው።
በዩናይትድ ስቴትስ የታወቁ የቲዮሎጂ ፕሮፌሰር የሆኑት ጆሴፍ ፍሌቸር ስለ አዲሱ ሥነ ምግባር እንዲህ ብለዋል:- “በዚህ ሥነ ምግባር መሠረት ከጋብቻ ውጭ የሚደረገውን የጾታ ግንኙነት የሚቃወም ነገር የለም። እንዲያውም በአንዳንድ ሁኔታዎች ጥሩ ሊሆን ይችላል።” በዩናይትድ ስቴትስ የሃይማኖት ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት ፍሬዴሪክ ሲ ውድ ለተማሪዎች እንዲህ በማለት ገልጸዋል:- “የወሲብ ድርጊቶችን የሚገዙ ሕጎች የሉም። እደግመዋለሁ፣ ምንም ዓይነት ሕግ የለም። ማድረግ አለባችሁ ወይም ማድረግ የለባችሁም የሚባል ምንም ነገር የለም።” ቲዮሎጂ ቱደይ ጥቅምት 1965 ገጽ 396
እነዚህን የመሰሉ የሥነ ምግባር አመለካከቶች በሰፊው የታወቁ ቢሆንም የይሖዋ ምሥክሮች ግን እነዚህ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር እንደሚጋጩና ተገቢ እንዳልሆኑ ያምናሉ። በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተመሠረተው ይህ አቋማችን በ1976 በታተመውና ጠባያችን በሥነ ምግባር ሥርዓቶች እንዴት እንደሚነካ በሚገልጸው ወጣትነትህን ከሁሉ በተሻለ መንገድ ተጠቀምበት በተባለው መጽሐፍ ላይ ተንጸባርቋል። አንድ ተመራማሪ ከ12 እስከ 19 ዓመት ዕድሜ ያላቸው 100 ተማሪዎች እንዲያነቡት ካደረገ በኋላ የተናገረው ሊጠቀስ የሚገባው ነው:- “በመጽሐፋችሁ ላይ የገለጻችሁት ዓይነት የሥነ ምግባር ደንብ ተግባራዊ ሊሆን የቻለበት ዘመን ይኖር ይሆናል። አሁን ግን መሥራቱን እጠራጠራለሁ። ይህ ትውልድ ከቀደሙት ትውልዶች ሁሉ ይበልጥ የሠለጠነ ነው።”
ይሁን እንጂ አዲሱን የሥነ ምግባር ደረጃ መያዝ ወጣቶችን ‘ይበልጥ የሰለጠኑ’ ያደረጋቸው መስሎ አይታየንም። በቅርቡ ከ13 እስከ
-