የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • አቅኚዎች ምን ዓይነት የትምህርት አጋጣሚዎች ተከፍተውላቸዋል?
    በዛሬው ጊዜ የይሖዋን ፈቃድ የሚያደርጉት እነማን ናቸው?
    • ትምህርት 14

      አቅኚዎች ምን ዓይነት የትምህርት አጋጣሚዎች ተከፍተውላቸዋል?

      የሙሉ ጊዜ አገልጋዮች በስብከቱ ሥራ ላይ

      ዩናይትድ ስቴትስ

      በጊልያድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት እየተማሩ ያሉ ተማሪዎች
      ለሚስዮናዊ አገልግሎት እየሰለጠኑ ያሉ ተማሪዎች

      ጊልያድ ትምህርት ቤት፣ ፓተርሰን፣ ኒው ዮርክ

      አንድ ሚስዮናዊ ባልና ሚስት ፓናማ ውስጥ ሲሰብኩ

      ፓናማ

      ቲኦክራሲያዊ ትምህርት ቤቶች ለረጅም ጊዜ የይሖዋ ምሥክሮች መለያ ሆነው ቆይተዋል። ሙሉ ጊዜያቸውን የስብከቱን ሥራ ለማከናወን የሚያውሉ ክርስቲያኖች ‘አገልግሎታቸውን በተሟላ ሁኔታ መፈጸም’ እንዲችሉ የሚረዷቸው ለየት ያሉ የትምህርት አጋጣሚዎች አሏቸው።—2 ጢሞቴዎስ 4:5

      የአቅኚነት አገልግሎት ትምህርት ቤት፦ አንድ የዘወትር አቅኚ በሙሉ ጊዜ አገልግሎት አንድ ዓመት ካሳለፈ በኋላ ስድስት ቀን የሚፈጅ ሥልጠና መውሰድ ይችላል፤ ትምህርት ቤቱ የሚካሄደው በአካባቢው ባለ የስብሰባ አዳራሽ ሊሆን ይችላል። የዚህ ትምህርት ቤት ዓላማ አቅኚዎች ወደ ይሖዋ ይበልጥ እንዲቀርቡ፣ በሁሉም የአገልግሎታቸው ዘርፎች ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ እንዲሁም በታማኝነት በአገልግሎታቸው መጽናት እንዲችሉ መርዳት ነው።

      የመንግሥቱ ወንጌላውያን ትምህርት ቤት፦ ሁለት ወር የሚፈጀው ይህ ትምህርት ቤት፣ የሚኖሩበትን አካባቢ ትተው ይበልጥ እርዳታ ወደሚያስፈልግበት ቦታ ለመሄድ ፈቃደኛ የሆኑ ተሞክሮ ያላቸው አቅኚዎችን ለማሠልጠን የተዘጋጀ ነው። እነዚህ አቅኚዎች በምድር ላይ ከኖሩት ወንጌላውያን ሁሉ የላቀውን ወንጌላዊ ይኸውም የኢየሱስ ክርስቶስን ምሳሌ በመከተል “እነሆኝ! እኔን ላከኝ!” የሚሉ ያህል ነው። (ኢሳይያስ 6:8፤ ዮሐንስ 7:29) ከሚኖሩበት አካባቢ ርቀው መሄዳቸው አኗኗራቸውን ቀላል ማድረግ ይጠይቅባቸው ይሆናል። የሚሄዱበት አካባቢ ባሕል፣ የአየር ጠባይ እንዲሁም ምግብ ከለመዱት ፈጽሞ የተለየ ሊሆን ይችላል። ምናልባትም አዲስ ቋንቋ መማር ያስፈልጋቸው ይሆናል። ትምህርት ቤቱ፣ ከ23 እስከ 65 ዓመት ባለው የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ነጠላ ወንድሞች፣ እህቶች እንዲሁም ባለትዳሮች በተመደቡበት ቦታ የሚያስፈልጓቸውን መንፈሳዊ ባሕርያት ብሎም ይሖዋና ድርጅቱ ይበልጥ እንዲጠቀሙባቸው የሚያስችሏቸውን ክህሎቶች እንዲያዳብሩ ይረዳቸዋል።

      ጊልያድ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት፦ “ጊልያድ” የሚለው የዕብራይስጥ ቃል “የምሥክሮች ክምር” የሚል ትርጉም አለው። ትምህርት ቤቱ ከተቋቋመ ከ1943 ወዲህ ከጊልያድ የተመረቁ ከ8,000 በላይ ተማሪዎች ሚስዮናውያን እንዲሆኑ የተላኩ ሲሆን “እስከ ምድር ዳር ድረስ” ውጤታማ የሆነ ምሥክርነት መስጠት ችለዋል። (የሐዋርያት ሥራ 13:47) ለምሳሌ ያህል፣ ሚስዮናውያን መጀመሪያ ወደ ፔሩ ሲላኩ በዚያች አገር አንድም ጉባኤ አልነበረም። አሁን ግን ከ1,000 የሚበልጡ ጉባኤዎች አሉ። ሚስዮናውያኖቻችን መጀመሪያ ወደ ጃፓን ሲሄዱ በአገሪቱ የነበሩት የይሖዋ ምሥክሮች አሥር አይሞሉም ነበር። አሁን ግን ከ200,000 በላይ ሆነዋል። በጊልያድ የሚሰጠው የአምስት ወር ሥልጠና ተማሪዎቹ የአምላክን ቃል ጥልቀት ባለው መንገድ እንዲያጠኑ ያስችላቸዋል። ልዩ አቅኚዎች፣ በመስክ የሚያገለግሉ ሚስዮናውያን፣ በቅርንጫፍ ቢሮዎች ውስጥ የሚሠሩ ወይም በወረዳ ሥራ የሚካፈሉ ክርስቲያኖች በትምህርት ቤቱ እንዲሠለጥኑ ይጋበዛሉ፤ በዚህ የሚሰጠው ጥልቀት ያለው ሥልጠና በዓለም ዙሪያ የሚከናወነውን ሥራ ለማጠናከር አስተዋጽኦ ያበረክታል።

      • የአቅኚነት አገልግሎት ትምህርት ቤት ዓላማ ምንድን ነው?

      • በመንግሥቱ ወንጌላውያን ትምህርት ቤት መሠልጠን የሚችሉት እነማን ናቸው?

  • ሽማግሌዎች ጉባኤውን የሚያገለግሉት እንዴት ነው?
    በዛሬው ጊዜ የይሖዋን ፈቃድ የሚያደርጉት እነማን ናቸው?
    • ትምህርት 15

      ሽማግሌዎች ጉባኤውን የሚያገለግሉት እንዴት ነው?

      አንድ ሽማግሌ ከጉባኤው አባላት ጋር ሲያወራ

      ፊንላንድ

      አንድ ሽማግሌ ጉባኤ ውስጥ ሲያስተምር

      ማስተማር

      ሽማግሌዎች የጉባኤውን አባላት ሲያበረታቱ

      እረኝነት

      አንድ ሽማግሌ በስብከቱ ሥራ ላይ

      መመሥከር

      በድርጅታችን ውስጥ ደሞዝ የሚከፈላቸው ቀሳውስት የሉንም። ከዚህ ይልቅ የክርስቲያን ጉባኤ በተቋቋመበት ጊዜ እንደተደረገው ሁሉ ዛሬም ብቃት ያላቸው የበላይ ተመልካቾች የአምላክን ‘ጉባኤ እንዲጠብቁ’ ይሾማሉ። (የሐዋርያት ሥራ 20:28) እነዚህ ሽማግሌዎች በመንፈሳዊ የጎለመሱ ወንዶች ናቸው፤ ሽማግሌዎች ጉባኤው በሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ግንባር ቀደም ሆነው የሚካፈሉ ከመሆኑም ሌላ “በግዴታ ሳይሆን በአምላክ ፊት በፈቃደኝነት . . . አግባብ ያልሆነ ጥቅም ለማግኘት በመመኘት ሳይሆን ለማገልገል በመጓጓት” ለጉባኤው እንደ እረኞች ሆነው ያገለግላሉ። (1 ጴጥሮስ 5:1-3) ሽማግሌዎች እኛን የሚጠቅሙ ምን ሥራዎችን ያከናውናሉ?

      ይንከባከቡናል እንዲሁም ይጠብቁናል። ሽማግሌዎች ለጉባኤው አባላት ቅዱስ ጽሑፋዊ መመሪያዎች የሚሰጡ ከመሆኑም ሌላ በመንፈሳዊ ሁኔታ አደጋ ላይ እንዳይወድቁ ጥበቃ ያደርጋሉ። አምላክ ይህን አስፈላጊ የሆነ ሥራ በአደራ እንደሰጣቸው ስለሚገነዘቡ ለሕዝቦቹ ደህንነትና ደስታ አስተዋጽኦ ለማበርከት ይጥራሉ እንጂ በእነሱ ላይ የበላይ ለመሆን አይሞክሩም። (2 ቆሮንቶስ 1:24) አንድ እረኛ በመንጋው ውስጥ የሚገኘውን እያንዳንዱን በግ በትጋት እንደሚንከባከብ ሁሉ ሽማግሌዎችም እያንዳንዱን የጉባኤ አባል በግለሰብ ደረጃ ለማወቅ ጥረት ያደርጋሉ።—ምሳሌ 27:23

      የአምላክን ፈቃድ ማድረግ የምንችልበትን መንገድ ያስተምሩናል። ሽማግሌዎች በየሳምንቱ የሚደረጉትን የጉባኤ ስብሰባዎች በመምራት እምነታችንን ያጠናክሩልናል። (የሐዋርያት ሥራ 15:32) በተጨማሪም እነዚህ ለአምላክ ያደሩ ወንዶች በወንጌላዊነቱ ሥራ ግንባር ቀደም በመሆን በሁሉም የአገልግሎት ዘርፎች አብረውን ይካፈላሉ፤ እንዲሁም ሥልጠና ይሰጡናል።

      በግለሰብ ደረጃ ያበረታቱናል። የጉባኤያችን ሽማግሌዎች መንፈሳዊነታችንን እንድናጠናክር በግለሰብ ደረጃ ለመርዳት ሲሉ በየቤታችን እየመጡ ወይም በስብሰባ አዳራሽ ውስጥ ከቅዱሳን መጻሕፍት ማጽናኛና ማበረታቻ ይሰጡናል።—ያዕቆብ 5:14, 15

      አብዛኞቹ ሽማግሌዎች በጉባኤ ውስጥ ከሚያከናውኑት ሥራ በተጨማሪ ጊዜያቸውንና ትኩረታቸውን የሚጠይቁ ሌሎች ኃላፊነቶች አሏቸው፤ ከእነዚህም መካከል ሰብዓዊ ሥራቸውና የቤተሰብ ኃላፊነታቸው ይገኙበታል። በመሆኑም እነዚህን ትጉ ወንድሞቻችንን ልናከብራቸው ይገባል።—1 ተሰሎንቄ 5:12, 13

      • ሽማግሌዎች በጉባኤ ውስጥ ምን ኃላፊነት አለባቸው?

      • ሽማግሌዎች በግለሰብ ደረጃ እንደሚያስቡልን የሚያሳዩት በምን መንገዶች ነው?

      ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት

      ሽማግሌ ሆነው ለማገልገል ብቁ የሚሆኑት እነማን ናቸው? ሽማግሌዎችና የጉባኤ አገልጋዮች ሊያሟሏቸው የሚገቡትን ቅዱስ ጽሑፋዊ ብቃቶች በ1 ጢሞቴዎስ 3:1-10, 12 እና በቲቶ 1:5-9 ላይ ማግኘት ትችላለህ።

  • የጉባኤ አገልጋዮች ምን ሚና ይጫወታሉ?
    በዛሬው ጊዜ የይሖዋን ፈቃድ የሚያደርጉት እነማን ናቸው?
    • ትምህርት 16

      የጉባኤ አገልጋዮች ምን ሚና ይጫወታሉ?

      አንድ የጉባኤ አገልጋይ ጽሑፍ ሲያከፋፍል

      ምያንማር

      አንድ የጉባኤ አገልጋይ መንፈሳዊ ትምህርት ሲሰጥ

      ክፍል ማቅረብ

      አንድ የጉባኤ አገልጋይ ስብሰባ ሲመራ

      የስምሪት ስብሰባ መምራት

      አንድ የጉባኤ አገልጋይ የመንግሥት አዳራሹን በመንከባከቡ ሥራ ላይ ሲካፈል

      የስብሰባ አዳራሹን መንከባከብ

      በጉባኤ ውስጥ በኃላፊነት የሚያገለግሉ ክርስቲያን ወንዶች በሁለት እንደሚከፈሉ መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል፤ እነሱም ‘ሽማግሌዎችና የጉባኤ አገልጋዮች’ ናቸው። (ፊልጵስዩስ 1:1) አብዛኛውን ጊዜ በእያንዳንዱ ጉባኤ ውስጥ እነዚህን ኃላፊነቶች የሚወጡ በርካታ ወንድሞች ይኖራሉ። ታዲያ የጉባኤ አገልጋዮች እኛን የሚጠቅሙ ምን ሥራዎችን ያከናውናሉ?

      የሽማግሌዎች አካልን ያግዛሉ። በየትኛውም ዕድሜ ላይ የሚገኙ የጉባኤ አገልጋዮች መንፈሳዊ አመለካከት ያላቸው፣ እምነት የሚጣልባቸውና በትጋት የሚሠሩ ወንድሞች ናቸው። ከድርጅታዊ አሠራር ጋር የተያያዙ እንዲሁም የስብሰባ አዳራሹን የሚመለከቱ ተደጋጋሚ ሆኖም አስፈላጊ ሥራዎችን ያከናውናሉ። የጉባኤ አገልጋዮች እነዚህን ሥራዎች በማከናወናቸው ሽማግሌዎች በማስተማርና በእረኝነት ሥራዎች ላይ ማተኮር ይችላሉ።

      ጠቃሚ የሆነ አገልግሎት ይሰጣሉ። አንዳንድ የጉባኤ አገልጋዮች፣ ወደ ስብሰባ ለሚመጡ ሁሉ ጥሩ አቀባበል እንዲያደርጉ አስተናጋጅ ሆነው ይመደባሉ። ሌሎች ደግሞ በድምፅ ወይም በጽሑፍ ክፍል ውስጥ ያገለግላሉ፤ የሒሳብ አገልጋይ ሆነው ይሠራሉ፤ አሊያም የጉባኤው አባላት የሚሰብኩባቸውን ክልሎች ያከፋፍላሉ። በተጨማሪም የስብሰባ አዳራሹ በአግባቡ እንዲያዝ በማድረግ ረገድ እርዳታ ያበረክታሉ። ከዚህም ሌላ የጉባኤ አገልጋዮች፣ አረጋውያንን እንዲረዱ ሽማግሌዎች ሊጠይቋቸው ይችላሉ። የጉባኤ አገልጋዮች ምንም ዓይነት ኃላፊነት ቢሰጣቸው ሥራቸውን በፈቃደኝነት ስለሚያከናውኑ ሁሉም የጉባኤው አባላት ሊያከብሯቸው ይገባል።—1 ጢሞቴዎስ 3:13

      ግሩም ምሳሌ የሚሆኑ ክርስቲያን ወንዶች ናቸው። ክርስቲያን ወንዶች፣ የጉባኤ አገልጋዮች እንዲሆኑ የሚሾሙት ጥሩ መንፈሳዊ ባሕርያት ስላሏቸው ነው። የጉባኤ አገልጋዮች በስብሰባዎች ላይ ክፍል በማቅረብ እምነታችንን ያጠናክሩልናል። በስብከቱ ሥራ በግንባር ቀደምትነት በመካፈል በቅንዓት እንድናገለግል ያነሳሱናል። ከሽማግሌዎች ጋር ተባብረው በመሥራት በጉባኤው ውስጥ ደስታና አንድነት እንዲኖር አስተዋጽኦ ያደርጋሉ። (ኤፌሶን 4:16) ውሎ አድሮ ደግሞ እነሱም ሽማግሌ ሆነው ለማገልገል የሚያስፈልገውን ብቃት ሊያሟሉ ይችላሉ።

      • የጉባኤ አገልጋዮች ሆነው የሚሾሙት ምን ዓይነት ወንዶች ናቸው?

      • አገልጋዮች የጉባኤው እንቅስቃሴ የተቀላጠፈ እንዲሆን የሚረዱት እንዴት ነው?

      ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት

      ስብሰባ ላይ ስትገኝ ጊዜ ወስደህ ከሽማግሌዎች ወይም ከጉባኤ አገልጋዮች መካከል ከአንዱ ጋር ለመተዋወቅ ጥረት አድርግ፤ በዚህ መንገድ ሁሉንም ሽማግሌዎችና የጉባኤ አገልጋዮች እንዲሁም ቤተሰቦቻቸውን በደንብ ማወቅ ትችላለህ።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ