የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • በዛሬው ጊዜ የበላይ አካሉ ሥራውን የሚያከናውነው እንዴት ነው?
    በዛሬው ጊዜ የይሖዋን ፈቃድ የሚያደርጉት እነማን ናቸው?
    • ትምህርት 20

      በዛሬው ጊዜ የበላይ አካሉ ሥራውን የሚያከናውነው እንዴት ነው?

      በመጀመሪያው መቶ ዘመን የነበረው የበላይ አካል

      የመጀመሪያው መቶ ዘመን የበላይ አካል

      በመጀመሪያው ዘመን የነበሩ ክርስቲያኖች ከበላይ አካሉ የተላከውን ደብዳቤ ሲያነቡ

      የበላይ አካሉ ደብዳቤ ሲነበብ

      በአንደኛው መቶ ዘመን በኢየሩሳሌም የሚገኙ ‘ሐዋርያትንና ሽማግሌዎችን’ ያቀፈ አንድ ትንሽ ቡድን መላውን የቅቡዓን ክርስቲያኖች ጉባኤ ወክሎ ትልቅ ቦታ የሚሰጣቸው ውሳኔዎችን የሚያስተላልፍ የበላይ አካል ሆኖ አገልግሏል። (የሐዋርያት ሥራ 15:2) የዚህ የበላይ አካል አባላት በአንድ ድምፅ ውሳኔ ማስተላለፍ የቻሉት በቅዱሳን መጻሕፍት ላይ ስለተወያዩና የመንፈስ ቅዱስን አመራር ስለተከተሉ ነበር። (የሐዋርያት ሥራ 15:25) ዛሬም ያለው የበላይ አካል የእነሱን ምሳሌ ይከተላል።

      አምላክ ፈቃዱን ለማድረግ በበላይ አካሉ ይጠቀማል። የበላይ አካል አባላት ሆነው የሚያገለግሉት ቅቡዓን ወንድሞች ለአምላክ ቃል ትልቅ ቦታ የሚሰጡ ሲሆን ከመንፈሳዊ ነገሮችም ሆነ ከሌሎች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ የረጅም ጊዜ ልምድ ያካበቱ ናቸው። እነዚህ ወንድሞች ዓለም አቀፉን የወንድማማች ማኅበር ስለሚመለከቱ ጉዳዮች ለመወያየት በየሳምንቱ ስብሰባ ያደርጋሉ። በአንደኛው መቶ ዘመን ይደረግ እንደነበረው ሁሉ መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት ያደረጉ መመሪያዎች የሚተላለፉት በደብዳቤዎች፣ በተጓዥ የበላይ ተመልካቾችና በሌሎች ወንድሞች አማካኝነት ነው። ይህም የአምላክ ሕዝቦች አስተሳሰባቸውም ሆነ ተግባራቸው አንድ ዓይነት እንዲሆን አስችሏል። (የሐዋርያት ሥራ 16:4, 5) የበላይ አካሉ የመንፈሳዊ ምግቦችን ዝግጅት እንዲሁም ወንድሞች ለኃላፊነት ቦታ የሚሾሙበትን ሁኔታ በበላይነት ይከታተላል፤ በተጨማሪም ለመንግሥቱ ስብከት ሥራ ቅድሚያ እንድንሰጥ ያበረታታናል።

      የበላይ አካሉ የአምላክን መንፈስ አመራር ይከተላል። የበላይ አካሉ መመሪያ ለማግኘት የጽንፈ ዓለሙ ሉዓላዊ ገዢ ወደሆነው ወደ ይሖዋና የጉባኤው ራስ ወደሆነው ወደ ኢየሱስ ዘወር ይላል። (1 ቆሮንቶስ 11:3፤ ኤፌሶን 5:23) የበላይ አካሉ አባላት ራሳቸውን የአምላክ ሕዝቦች መሪዎች እንደሆኑ አድርገው አይቆጥሩም። እነሱም ሆኑ የቀሩት ቅቡዓን ክርስቲያኖች “ምንጊዜም በጉ [ኢየሱስ] በሄደበት ሁሉ ይከተሉታል።” (ራእይ 14:4) የበላይ አካሉ አባላት ስለ እነሱ ለምናቀርበው ጸሎት አመስጋኞች ናቸው።

      • በመጀመሪያው መቶ ዘመን የበላይ አካል አባላት የነበሩት እነማን ናቸው?

      • በዛሬው ጊዜ የበላይ አካሉ የአምላክን አመራር ለማግኘት ምን ያደርጋል?

      ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት

      በመጀመሪያው መቶ ዘመን የነበረው የበላይ አካል በቅዱሳን መጻሕፍትና በመንፈስ ቅዱስ አመራር በመታገዝ በአንድ ጉዳይ ላይ ተወያይቶ እልባት መስጠት የቻለው እንዴት እንደሆነ ለማወቅ የሐዋርያት ሥራ 15:1-35⁠ን አንብብ።

  • ቤቴል ምንድን ነው?
    በዛሬው ጊዜ የይሖዋን ፈቃድ የሚያደርጉት እነማን ናቸው?
    • ትምህርት 21

      ቤቴል ምንድን ነው?

      ቤቴል ውስጥ በሥነ ጥበብ ክፍል እየሠሩ ያሉ ሁለት የይሖዋ ምሥክሮች

      የሥነ ጥበብ ክፍል፣ ዩናይትድ ስቴትስ

      በጀርመን ቤቴል የሕትመት ክፍል ውስጥ  እየሠራ ያለ የይሖዋ ምሥክር

      ጀርመን

      በኬንያ ቤቴል የልብስ ንጽሕና ክፍል ውስጥ እየሠራች ያለች አንዲት የይሖዋ ምሥክር

      ኬንያ

      በኮሎምቢያ ቤቴል የመመገቢያ አዳራሽ ውስጥ እየሠሩ ያሉ አስተናጋጆች

      ኮሎምቢያ

      ቤቴል የሚለው የዕብራይስጥ ስም “የአምላክ ቤት” የሚል ትርጉም አለው። (ዘፍጥረት 28:17, 19 የግርጌ ማስታወሻ) የይሖዋ ምሥክሮች ለስብከቱ ሥራ አመራርና ድጋፍ ለመስጠት የሚጠቀሙባቸው በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ሕንፃዎች በዚህ መጠሪያ መሰየማቸው የተገባ ነው። የበላይ አካሉ የሚገኘው በኒው ዮርክ ግዛት፣ ዩናይትድ ስቴትስ ባለው ዋና መሥሪያ ቤት ሲሆን በበርካታ አገሮች የሚገኙትን ቅርንጫፍ ቢሮዎች እንቅስቃሴ ይከታተላል። በእነዚህ ቅርንጫፍ ቢሮዎች ውስጥ የሚያገለግሉት ክርስቲያኖች በሙሉ የቤቴል ቤተሰብ በመባል ይታወቃሉ። እነዚህ ክርስቲያኖች ልክ እንደ ቤተሰብ አብረው ይኖራሉ፣ አብረው ይሠራሉ እንዲሁም መጽሐፍ ቅዱስን አብረው ያጠናሉ።—መዝሙር 133:1

      የራሱን ጥቅም መሥዋዕት የሚያደርግ ቤተሰብ የሚኖርበት ልዩ ቦታ። በእያንዳንዱ ቤቴል ውስጥ ሙሉ ጊዜያቸውን የአምላክን ፈቃድ ለማድረግና ከመንግሥቱ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ለማከናወን የሚያውሉ ክርስቲያን ወንዶችና ሴቶች ይገኛሉ። (ማቴዎስ 6:33) የሚኖሩበት ክፍልና ምግብ ይሟላላቸዋል፤ እንዲሁም የግል ወጪያቸውን ለመሸፈን የሚያግዛቸው አነስተኛ አበል ይሰጣቸዋል። ከዚህ ውጭ ግን አንዳቸውም ቢሆኑ ደሞዝ አይከፈላቸውም። በቤቴል ውስጥ የሚገኙ ክርስቲያኖች በሙሉ የራሳቸው የሥራ ምድብ ያላቸው ሲሆን አንዳንዶቹ ቢሮ ውስጥ ሌሎቹ ደግሞ ወጥ ቤት ወይም መመገቢያ አዳራሽ ውስጥ እንዲሠሩ ይመደባሉ። በሕትመትና በመጻሕፍት መጠረዣ ክፍል፣ በቤት ጽዳት፣ በልብስ እጥበት፣ በጥገና ክፍል እንዲሁም በሌሎች ክፍሎች ውስጥ የሚሠሩም አሉ።

      የስብከቱን ሥራ የሚደግፉ ሰዎች የሚገኙበት ሥራ የበዛበት ቦታ። የሁሉም ቤቴሎች ዋነኛ ዓላማ የመጽሐፍ ቅዱስን እውነት በተቻለ መጠን ለብዙ ሰዎች ማዳረስ ነው። ይህ ብሮሹር ለዚህ አንድ ምሳሌ ነው። የተጻፈው በበላይ አካሉ አመራር ሲሆን በኤሌክትሮኒክ ቅጂ ተዘጋጅቶ በመላው ዓለም ወደሚገኙ በመቶዎች የሚቆጠሩ የትርጉም ቡድኖች ተሰራጨ፤ ከዚያም ከፍተኛ ፍጥነት ባላቸው የተለያዩ የቤቴል ማተሚያ ቤቶች ከታተመ በኋላ ከ110,000 በላይ ወደሆኑት ጉባኤዎች ተላከ። በእያንዳንዱ ሂደት ላይ የቤቴል ቤተሰቦች እጅግ አጣዳፊ ለሆነው ምሥራቹን የመስበክ ሥራ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ያበረክታሉ።—ማርቆስ 13:10

      • በቤቴል የሚያገለግሉት ምን ዓይነት ሰዎች ናቸው? ምን ዝግጅትስ ይደረግላቸዋል?

      • በእያንዳንዱ ቤቴል የሚከናወነው እንቅስቃሴ የትኛውን አጣዳፊ ሥራ ይደግፋል?

  • በቅርንጫፍ ቢሮ ውስጥ ምን ዓይነት ሥራ ይከናወናል?
    በዛሬው ጊዜ የይሖዋን ፈቃድ የሚያደርጉት እነማን ናቸው?
    • ትምህርት 22

      በቅርንጫፍ ቢሮ ውስጥ ምን ዓይነት ሥራ ይከናወናል?

      በሰለሞን ደሴቶች ቅርንጫፍ ቢሮ የሚካሄደውን ሥራ የሚያደራጁ ወንድሞች

      የሰለሞን ደሴቶች

      በካናዳ ቅርንጫፍ ቢሮ ውስጥ የሚያገለግል አንድ የይሖዋ ምሥክር

      ካናዳ

      ጽሑፎችን የሚያጓጉዙ ከባድ መኪናዎች

      ደቡብ አፍሪካ

      የቤቴል ቤተሰብ አባላት በተለያዩ ክፍሎች ውስጥ ተመድበው የሚያገለግሉ ሲሆን በአገራቸው ወይም በሌሎች አገሮች ከሚከናወነው የስብከት እንቅስቃሴ ጋር የተያያዙ ሥራዎችን ያከናውናሉ። ቤቴላውያን በትርጉም ቡድኖች ውስጥ፣ በመጽሔቶች ሕትመት፣ በመጻሕፍት ጥረዛና በጽሑፍ ማቆያ እንዲሁም በድምፅ/ምስል ቀረጻ ክፍል ውስጥ ይሠራሉ፤ አሊያም በቅርንጫፍ ቢሮው ሥር ካሉ አካባቢዎች ጋር የተያያዙ ሌሎች ሥራዎችን ያከናውናሉ።

      የቅርንጫፍ ኮሚቴ፣ ሥራውን በበላይነት ይከታተላል። የበላይ አካሉ የእያንዳንዱን ቅርንጫፍ ቢሮ እንቅስቃሴ የሚከታተል የቅርንጫፍ ኮሚቴ ይሾማል፤ ይህ ኮሚቴ ሦስት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ብቃት ያላቸው ሽማግሌዎችን ያቀፈ ነው። የቅርንጫፍ ኮሚቴው በሥሩ በሚገኙት አገሮች ስላለው እንቅስቃሴና ስለተፈጠሩ ችግሮች ለበላይ አካሉ በየጊዜው ያሳውቃል። የበላይ አካሉም እነዚህን ሪፖርቶች መሠረት በማድረግ ወደፊት በሚወጡ ጽሑፎች እንዲሁም በጉባኤና በትላልቅ ስብሰባዎች ላይ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባው ጉዳይ ምን እንደሆነ ይወስናል። የበላይ አካሉ ተወካዮች ቅርንጫፍ ቢሮዎችን እንዲጎበኙ በየጊዜው የሚላኩ ሲሆን እነዚህ የበላይ ተመልካቾች ለቅርንጫፍ ኮሚቴ አባላት ሥራቸውን ስለሚያከናውኑበት መንገድ መመሪያ ይሰጧቸዋል። (ምሳሌ 11:14) በጉብኝቱ ወቅት በቅርንጫፍ ቢሮው ክልል ውስጥ ለሚኖሩት ወንድሞች ማበረታቻ ለመስጠት ልዩ ፕሮግራም የሚዘጋጅ ሲሆን በዚህ ዝግጅት ላይ የዋና መሥሪያ ቤት ተወካዩ ንግግር ያቀርባል።

      ቅርንጫፍ ቢሮው በሥሩ ያሉ ጉባኤዎችን ይደግፋል። በቅርንጫፍ ቢሮ ውስጥ የሚገኙ ኃላፊነት ያላቸው ወንድሞች የአዳዲስ ጉባኤዎችን መቋቋም ያጸድቃሉ። በተጨማሪም እነዚህ ወንድሞች በቅርንጫፍ ቢሮው ክልል ውስጥ የሚገኙ አቅኚዎች፣ ሚስዮናውያንና የወረዳ የበላይ ተመልካቾች ከሚያከናውኑት ሥራ ጋር በተያያዘ መመሪያ ይሰጣሉ። ትላልቅ ስብሰባዎችን ያደራጃሉ፣ የአዳዲስ ስብሰባ አዳራሾችን ግንባታ ያስተባብራሉ እንዲሁም ለእያንዳንዱ ጉባኤ የሚያስፈልገው ጽሑፍ መላኩን ይከታተላሉ። በቅርንጫፍ ቢሮ ውስጥ የሚከናወኑ ሥራዎች በሙሉ የስብከቱ ሥራ ሥርዓት ባለው መልኩ እንዲከናወን አስተዋጽኦ ያበረክታሉ።—1 ቆሮንቶስ 14:33, 40

      • የቅርንጫፍ ኮሚቴዎች የበላይ አካሉን የሚያግዙት እንዴት ነው?

      • በቅርንጫፍ ቢሮ ውስጥ ምን ዓይነት ሥራ ይከናወናል?

      ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት

      ማንኛውም ሰው ከሰኞ እስከ ዓርብ ባሉት ቀናት አስጎብኚ ተመድቦለት ቅርንጫፍ ቢሮዎቻችንን መጎብኘት ይችላል። አንተም ቤቴልን እንድትጎበኝ እንጋብዝሃለን። ለጉብኝት በምትሄድበት ጊዜ ስብሰባ ስትሄድ የሚኖርህ ዓይነት አለባበስ ይኑርህ። ቤቴልን መጎብኘትህ መንፈሳዊ ጥቅም ያስገኝልሃል።

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ