የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w16 ሚያዝያ ገጽ 32
  • የአንባቢያን ጥያቄዎች

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የአንባቢያን ጥያቄዎች
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2016
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ጥንታዊ ማኅተሞች ምን ዓይነት ነበሩ?
    ተጨማሪ ርዕሰ ጉዳዮች
  • “ይህ መንፈስ ራሱ . . . ይመሠክራል”
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020
  • የአንባቢያን ጥያቄዎች
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2007
  • መንፈሱ ከመንፈሳችን ጋር ሆኖ ይመሠክራል
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2016
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2016
w16 ሚያዝያ ገጽ 32

የአንባቢያን ጥያቄዎች

እያንዳንዱ ቅቡዕ ክርስቲያን ከአምላክ የሚቀበለው “ማረጋገጫ” እና ‘ማኅተም’ ምንድን ነው?—2 ቆሮ. 1:21, 22 ግርጌ

[በገጽ 32 ላይ የሚገኝ ሥዕል]

በጥንት ዘመን የአንድን ሰነድ ትክክለኛነት ለማረጋገጥ፣ የማኅተም ቀለበትን በጭቃ ወይም በሰም ላይ በመጫን ምልክት ይደረግበት ነበር

ማረጋገጫ፦ አንድ የማመሳከሪያ ጽሑፍ እንደሚገልጸው በ2 ቆሮንቶስ 1:22 ላይ “ማረጋገጫ” ተብሎ የተተረጎመው የግሪክኛ ቃል “ከሕግና ከንግድ ጋር በተያያዘ የሚሠራበት” ነው፤ ትርጉሙም “የመጀመሪያ ክፍያ፣ መያዣ፣ ቀብድ ማለት ሲሆን አንድ ነገር የተገዛበትን ዋጋ በተወሰነ መጠን በቅድሚያ በመክፈል የዕቃውን ሕጋዊ ባለቤትነት ለማረጋገጥ ወይም አንድን ውል ሕጋዊ ለማድረግ ያስችላል።” ይሖዋ ለቅቡዓን ሽልማት እንደሚያገኙ ማረጋገጫ ሰጥቷቸዋል፤ በ2 ቆሮንቶስ 5:1-5 ላይ እንደተገለጸው ቅቡዓኑ፣ ሙሉውን ክፍያ ወይም ሽልማት ሲያገኙ የማይበሰብስ ሰማያዊ አካል ይለብሳሉ። ሽልማቱ ያለመሞት ባሕርይ ማግኘትንም ይጨምራል።—1 ቆሮ. 15:48-54

በዘመናዊው ግሪክኛ፣ አንድ ሰው ሲታጭ የሚያደርገውን ቀለበት ለማመልከት የሚሠራበት ቃል “ማረጋገጫ” ተብሎ ከተተረጎመው ቃል ጋር ተዛማጅነት አለው። ይህ መሆኑም ተገቢ ነው፤ ምክንያቱም ቅቡዓን፣ የክርስቶስ ምሳሌያዊ ሚስት እንደሆኑ ተደርገው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተገልጸዋል።—2 ቆሮ. 11:2፤ ራእይ 21:2, 9

ማኅተም፦ በጥንት ዘመን ማኅተም የአንድን ነገር ባለቤትነትና ትክክለኛነት ለማመልከት ወይም ስምምነትን ለማረጋገጥ እንደ ፊርማ ሆኖ ያገለግል ነበር። ቅቡዓን ክርስቲያኖች፣ የአምላክ ንብረት መሆናቸውን ለማሳየት በምሳሌያዊ ሁኔታ በመንፈስ ቅዱስ ‘ታትመዋል’ ወይም ምልክት ተደርጎባቸዋል። (ኤፌ. 1:13, 14) ይሁንና ይህ የመጨረሻው ማኅተም አይደለም፤ አንድ ግለሰብ የመጨረሻው ማኅተም የሚደረግበት በታማኝነት ከመሞቱ ትንሽ ቀደም ብሎ አሊያም ታላቁ መከራ ከመምጣቱ ከተወሰነ ጊዜ በፊት ነው።—ኤፌ. 4:30፤ ራእይ 7:2-4

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ