የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • አብርሃምና ሣራ አምላክን ታዘዋል
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
    • አብርሃምና ሣራ ዑርን ለቅቀው ለመውጣት ዕቃቸውን ሲያዘጋጁ

      ትምህርት 8

      አብርሃምና ሣራ አምላክን ታዘዋል

      በባቤል አቅራቢያ የምትገኝ ዑር የምትባል አንዲት ከተማ ነበረች፤ በከተማዋ የሚኖሩ ሰዎች ይሖዋን ሳይሆን ሌሎች አማልክትን ያመልኩ ነበር። ሆኖም በዚህች ከተማ የሚኖር ይሖዋን ብቻ የሚያመልክ አንድ ሰው ነበር። ይህ ሰው አብርሃም ይባላል።

      ይሖዋ አብርሃምን ‘ቤትህንና ዘመዶችህን ትተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ሂድ’ አለው። ከዚያም አምላክ እንዲህ ብሎ ቃል ገባለት፦ ‘ብዙ ሕዝብ ትሆናለህ፤ እንዲሁም በአንተ አማካኝነት ለምድር ሕዝቦች ሁሉ ጥሩ ነገር አደርግላቸዋለሁ።’

      አብርሃም፣ ይሖዋ ወዴት እንደሚልከው ባያውቅም በይሖዋ ታምኗል። ስለዚህ አብርሃም፣ ሚስቱ ሣራ፣ አባቱ ታራ እንዲሁም የወንድሙ ልጅ ሎጥ ዕቃቸውን ይዘው በታዛዥነት ረጅሙን ጉዞ ጀመሩ።

      አብርሃምና ቤተሰቡ ይሖዋ ሊያሳያቸው ወደፈለገው ቦታ ሲደርሱ አብርሃም 75 ዓመቱ ነበር። ያ ቦታ የከነአን ምድር ይባል ነበር። እዚያ ከደረሱ በኋላ አምላክ አብርሃምን አነጋገረው፤ ‘ይህን የምታየውን ቦታ ሁሉ ለልጆችህ እሰጣቸዋለሁ’ ብሎ ቃል ገባለት። አብርሃምና ሣራ ግን አርጅተው የነበረ ሲሆን ምንም ልጅ አልነበራቸውም። ታዲያ ይሖዋ የገባውን ቃል የሚፈጽመው እንዴት ነው?

      አብርሃምና ሣራ ወደ ከነአን ሲጓዙ

      “አብርሃም . . . ወደፊት ርስት አድርጎ ወደሚቀበለው ስፍራ በመሄድ በእምነት ታዘዘ፤ ወዴት እንደሚሄድ ባያውቅም ይኖርበት የነበረውን ስፍራ ለቆ ወጣ።”—ዕብራውያን 11:8

      ጥያቄ፦ ይሖዋ አብርሃምን ምን እንዲያደርግ ጠየቀው? ይሖዋ ለአብርሃም ምን ብሎ ቃል ገባለት?

      ዘፍጥረት 11:29–12:9፤ የሐዋርያት ሥራ 7:2-4፤ ገላትያ 3:6፤ ዕብራውያን 11:8

  • በመጨረሻ ልጅ ወለዱ!
    ከመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች ምን ትማራለህ?
    • መላእክቱ አብርሃምን ሲያነጋግሩት ሣራ ድንኳን ውስጥ ሆና ስትሰማ

      ትምህርት 9

      በመጨረሻ ልጅ ወለዱ!

      አብርሃምና ሣራ ተጋብተው ለረጅም ጊዜ ኖረዋል። በዑር የነበራቸውን ምቹ ቤት ትተው በድንኳን እየኖሩ ነበር። ሆኖም ሣራ በይሖዋ ትታመን ስለነበር አላጉረመረመችም።

      ሣራ ልጅ ማግኘት በጣም ትፈልግ ስለነበር አብርሃምን ‘አገልጋዬ አጋር ልጅ ብትወልድ ልጁ እንደ ራሴ ልጅ ይሆናል’ አለችው። ከጊዜ በኋላ አጋር ወንድ ልጅ ወለደች። የልጁ ስም እስማኤል ይባላል።

      ሣራ እርጉዝ ሆና

      ከብዙ ዓመታት በኋላ ማለትም አብርሃም 99 ዓመት፣ ሣራ ደግሞ 89 ዓመት ሲሆናቸው ሦስት እንግዶች ወደ እነአብርሃም ቤት መጡ። አብርሃም እንግዶቹን ዛፍ ሥር እንዲያርፉና ምግብ እንዲበሉ ጠየቃቸው። እነዚህ እንግዶች እነማን እንደሆኑ ታውቃለህ? መላእክት ነበሩ! እነሱም አብርሃምን ‘በሚቀጥለው ዓመት በዚህ ጊዜ ሚስትህ ወንድ ልጅ ትወልዳለች’ አሉት። ሣራ ድንኳኑ ውስጥ ሆና የሚሉትን ትሰማ ነበር። ይህን ስትሰማ ‘አሁን እንዲህ ካረጀሁ በኋላ ልጅ መውለድ እችላለሁ?’ ብላ በማሰብ ሳቀች።

      በቀጣዩ ዓመት ልክ የይሖዋ መልአክ እንደተናገረው ሣራ ወንድ ልጅ ወለደች። አብርሃም ልጁን ይስሐቅ ብሎ ስም አወጣለት፤ ይስሐቅ ማለት “ሳቅ” ማለት ነው።

      ይስሐቅ አምስት ዓመት አካባቢ ሲሆነው ሣራ፣ እስማኤል በይስሐቅ ላይ ሲያሾፍበት አየች። ልጇን ለመጠበቅ ስትል አጋርንና እስማኤልን እንዲያባርራቸው አብርሃምን ጠየቀችው። አብርሃም መጀመሪያ ላይ እንደዚህ ማድረግ አልፈለገም ነበር። ሆኖም ይሖዋ ለይስሐቅ ጥበቃ ማድረግ ስለፈለገ አብርሃምን እንዲህ አለው፦ ‘ሣራ የምትልህን ስማ። እስማኤልን እኔ እንከባከበዋለሁ። የገባሁልህ ቃል የሚፈጸመው ግን በይስሐቅ በኩል ነው።’

      አጋርና እስማኤል ሲሄዱ ሣራና ይስሐቅ ቆመው እየተመለከቷቸው ነው

      “ሣራም የተስፋን ቃል የሰጠው እሱ ታማኝ እንደሆነ አድርጋ ስላሰበች . . . ዘር ለመፀነስ በእምነት ኃይል አገኘች።”—ዕብራውያን 11:11

      ጥያቄ፦ ሣራ መላእክቱ ለአብርሃም ምን ብለው ሲነግሩት ሰማች? ይሖዋ ለይስሐቅ ጥበቃ ያደረገለት እንዴት ነው?

      ዘፍጥረት 16:1-4, 15, 16፤ 17:25-27፤ 18:1-15፤ 21:1-14፤ ዕብራውያን 11:11

አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ