የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ijwyp ርዕስ 109
  • ልጠመቅ?—ክፍል 1፦ የጥምቀት ትርጉም

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ልጠመቅ?—ክፍል 1፦ የጥምቀት ትርጉም
  • የወጣቶች ጥያቄ
  • ንዑስ ርዕሶች
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • ጥምቀት ምንድን ነው?
  • ራስን መወሰን ምንድን ነው?
  • መጠመቅ አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?
  • ለመጠመቅ ዝግጁ ነህ?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2020
  • ጥምቀት—ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ግብ!
    ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ
  • ወጣቶች—ለመጠመቅ ዝግጁ ናችሁ?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2016
  • ጥምቀት—ከክርስቲያኖች የሚጠበቅ ብቃት
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (የጥናት እትም)—2018
ለተጨማሪ መረጃ
የወጣቶች ጥያቄ
ijwyp ርዕስ 109
አንድ ወጣት በይሖዋ ምሥክሮች የክልል ስብሰባ ላይ ገንዳ ውስጥ ሲጠመቅ።

የወጣቶች ጥያቄ

ልጠመቅ?—ክፍል 1፦ የጥምቀት ትርጉም

በየዓመቱ በይሖዋ ምሥክር ቤተሰብ ውስጥ ያደጉ በርካታ ወጣቶች ይጠመቃሉ። አንተስ ይህን እርምጃ ለመውሰድ እያሰብክ ነው? ከሆነ በመጀመሪያ ራስን መወሰን እና መጠመቅ ምን ትርጉም እንዳለው መረዳት ይኖርብሃል።

  • ጥምቀት ምንድን ነው?

  • ራስን መወሰን ምንድን ነው?

  • መጠመቅ አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?

  • እኩዮችህ ምን ይላሉ?

  • የተሳሳተ አመለካከት እና እውነታ

ጥምቀት ምንድን ነው?

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተጠቀሰው ጥምቀት የሚያመለክተው በውኃ መረጨትን ሳይሆን ሙሉ በሙሉ ውኃ ውስጥ መጥለቅን ነው፤ ይህ ደግሞ ልዩ ትርጉም አለው።

  • ስትጠመቅ ውኃ ውስጥ መጥለቅህ ከዚህ በኋላ የምትኖረው ራስህን ለማስደሰት እንዳልሆነ ለሰዎች ያሳያል።

  • ከውኃው መውጣትህ አምላክን በማስደሰት ላይ ያተኮረ አዲስ ሕይወት መምራት እንደጀመርክ ያሳያል።

መጠመቅህ ትክክል ወይም ስህተት የሆነውን ነገር በተመለከተ መሥፈርት የማውጣት ሥልጣን ያለው ይሖዋ እንደሆነ አምነህ መቀበልህን በይፋ ያሳያል፤ በተጨማሪም ይሖዋ የሚጠብቅብህን ነገር በፈቃደኝነት ለማድረግ ቃል መግባትህን ለሰዎች ታሳያለህ።

ሊታሰብበት የሚገባ ነጥብ፦ ይሖዋን በመታዘዝ ላይ ያተኮረ ሕይወት ለመምራት በሕዝብ ፊት ቃል መግባትህ አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው? አንደኛ ዮሐንስ 4:19⁠ን እና ራእይ 4:11⁠ን ተመልከት።

ራስን መወሰን ምንድን ነው?

ከመጠመቅህ በፊት ብቻህን ሆነህ ራስህን ለይሖዋ መወሰን ይኖርብሃል። ይህን ማድረግ የምትችለው እንዴት ነው?

በግልህ ወደ ይሖዋ ጸሎት በማቅረብ እሱን ለዘላለም ለማገልገል ቃል መግባትህን እንዲሁም ምንም ዓይነት ሁኔታ ቢያጋጥምህ ወይም ሌሎች ምንም ቢያደርጉ የእሱን ፈቃድ እንደምታደርግ ትነግረዋለህ።

ጥምቀት ብቻህን ሆነህ ያደረግከውን ይህን ውሳኔ ለሰዎች የምታሳይበት ሥነ ሥርዓት ነው። መጠመቅህ ራስህን መካድህንና ከዚህ በኋላ የይሖዋ ንብረት መሆንህን ለሌሎች ያሳያል።—ማቴዎስ 16:24

ሊታሰብበት የሚገባ ነጥብ፦ የይሖዋ ንብረት መሆንህ የተሻለ ሕይወት እንድትመራ የሚረዳህ እንዴት ነው? ኢሳይያስ 48:17, 18⁠ን እና ዕብራውያን 11:6⁠ን ተመልከት።

መጠመቅ አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?

ኢየሱስ፣ መጠመቅ ከደቀ መዛሙርቱ የሚጠበቅ ብቃት እንደሆነ ገልጿል። (ማቴዎስ 28:19, 20) ስለዚህ ዛሬም ጥምቀት ከክርስቲያኖች የሚጠበቅ ብቃት ነው። እንዲያውም ጥምቀት ለመዳን አስፈላጊ እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ይገልጻል።—1 ጴጥሮስ 3:21

ሆኖም ለመጠመቅ የሚያነሳሳህ ለይሖዋ ያለህ ፍቅርና አድናቆት ሊሆን ይገባል። እንደ መዝሙራዊው ዓይነት አመለካከት ሊኖርህ ይገባል፤ መዝሙራዊው እንዲህ በማለት ጽፏል፦ “ላደረገልኝ መልካም ነገር ሁሉ ለይሖዋ ምን እመልስለታለሁ? [የይሖዋን] ስም እጠራለሁ። . . . ስእለቴን ለይሖዋ እፈጽማለሁ።”—መዝሙር 116:12-14

ሊታሰብበት የሚገባ ነጥብ፦ ይሖዋ ምን መልካም ነገር አድርጎልሃል? ምን ልትመልስለትስ ትችላለህ? ዘዳግም 10:12, 13⁠ን እና ሮም 12:1⁠ን ተመልከት።

እኩዮችህ ምን ይላሉ?

ሚጂን።

“ራስን መወሰን ማለት ለይሖዋ ቃል መግባት ማለት ነው፤ ይህ ደግሞ በቁም ነገር ሊታይ የሚገባው ነገር ነው። ሆኖም ራሳችንን ለይሖዋ ከወሰንን በኋላ የምንመራው ሕይወት በበረከት የተሞላ ነው። ምክንያቱም ራሳችንን ልንንከባከብ ከምንችለው በላይ ይሖዋ ይንከባከበናል።”—ሚጂን

ኤምበር።

“ይሖዋ እስካሁንም አንተን እንደሚወድህ አሳይቷል። ስትጠመቅ አንተም እሱን ከልብህ እንደምትወደው ታሳያለህ። መጠመቅ ትልቅ መብት ነው፤ ብዙ በረከትም ያስገኛል!”—ኤምበር

ጁሊያን።

“ልታደርጓቸው ከምትችሏቸው ውሳኔዎች ሁሉ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ራሳችሁን ለአምላክ ለመወሰንና ለመጠመቅ የምታደርጉት ውሳኔ ነው። ሆኖም ይህ ሊያስፈራችሁ አይገባም። ዝግጁ እስከሆናችሁና ይህን ውሳኔ ለማድረግ ያነሳሳችሁ ምክንያት ተገቢ እስከሆነ ድረስ ጥምቀት በሕይወታችሁ ከምታደርጓቸው ውሳኔዎች ሁሉ የተሻለው ነው።”—ጁሊያን

የተሳሳተ አመለካከት እና እውነታ

የተሳሳተ አመለካከት — ለመጠመቅ የሚያስችል ብስለት ያላቸው አዋቂዎች ብቻ ናቸው።

እውነታው — የአንድ ሰው ብስለት በዋነኝነት የተመካው በዕድሜው ላይ ሳይሆን ግለሰቡ ለይሖዋ ባለው ፍቅርና እሱን ለመታዘዝ ባለው ተነሳሽነት ላይ ነው። ዮሴፍ፣ ሳሙኤል እና ኢዮስያስ ገና በልጅነታቸው እንዲህ ያለ ብስለት አሳይተዋል። በዛሬው ጊዜ ያሉ በርካታ ወጣቶችም እንዲህ ያለ ብስለት ያሳያሉ።

መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? “ሕፃን እንኳ ባሕርይው ንጹሕና ትክክል መሆኑ በአድራጎቱ ይታወቃል።”—ምሳሌ 20:11

የተሳሳተ አመለካከት — ጓደኞችህ ከተጠመቁ አንተም ልትጠመቅ ይገባል።

እውነታው — ራስን መወሰን እና መጠመቅ በፈቃደኝነት ሊደረግ የሚገባው የግል ውሳኔ ነው። የሆነ ዕድሜ ላይ ስለደረስክ፣ እኩዮችህ ሲጠመቁ ስላየህ ወይም ሌሎች እንደሚጠብቁብህ ስለተሰማህ ብቻ ይህን እርምጃ ልትወስድ አይገባም።

መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? “[የአምላክ ሕዝብ] በገዛ ፈቃዱ ራሱን ያቀርባል።”—መዝሙር 110:3

የተሳሳተ አመለካከት — እስካልተጠመቅክ ድረስ ብታጠፋም አትጠየቅም።

እውነታው — በይሖዋ ፊት ተጠያቂ የምትሆነው ስትጠመቅ ሳይሆን በእሱ ዓይን ትክክልና ስህተት የሆነውን ነገር ስታውቅ ነው።

መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? “አንድ ሰው ትክክል የሆነውን ነገር እንዴት ማድረግ እንዳለበት እያወቀ ሳያደርገው ቢቀር ኃጢአት ይሆንበታል።”—ያዕቆብ 4:17

ጠቃሚ ምክር፦ ራስን መወሰንና መጠመቅ የሚያስፈራህ ከሆነ እንዲህ የሚሰማህ ለምን እንደሆነ ለማወቅ እንዲሁም ፍርሃትህን ለማሸነፍ አንዳንድ እርምጃዎችን መውሰድ ትችላለህ። ወጣቶች የሚጠይቋቸው ጥያቄዎችና ተግባራዊ መሆን የሚችሉ መልሶች፣ ጥራዝ 2 የተባለውን መጽሐፍ ምዕራፍ 37⁠ን ማንበብህ እንዲህ ለማድረግ ይረዳሃል።

ክለሳ፦ መጠመቅ አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?

  • ኢየሱስ፣ መጠመቅ ከደቀ መዛሙርቱ የሚጠበቅ ብቃት እንደሆነ ገልጿል።

  • ጥምቀት ለመዳን አስፈላጊ ነው።

  • ራስን ወስኖ በመጠመቅ የይሖዋ አገልጋይ መሆን ትልቅ መብት ነው።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ