የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ijwbq ርዕስ 54
  • ሰዎች የሚሞቱት ለምንድን ነው?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • ሰዎች የሚሞቱት ለምንድን ነው?
  • የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
  • ንዑስ ርዕሶች
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?
  • ኢየሱስ ያድናል—እንዴት?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2001
  • ኢየሱስ የሞተው ለምንድን ነው?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
  • አዳምና ሔዋን የሠሩት ኃጢአት ምን ነበር?
    የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
  • ኢየሱስ የተሠቃየውና የሞተው ለምንድን ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ (ለሕዝብ የሚሰራጭ)—2016
ለተጨማሪ መረጃ
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎችና መልሶቻቸው
ijwbq ርዕስ 54

ሰዎች የሚሞቱት ለምንድን ነው?

መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል?

በተለይ የቅርብ ወዳጆቻችንን በሞት ስናጣ ሰዎች ለምን እንደሚሞቱ መጠየቃችን የተለመደ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ “ሞት የሚያስከትለው መንደፊያ ኃጢአት ነው” ይላል።​—1 ቆሮንቶስ 15:56

ሁሉም ሰዎች ኃጢአተኛ የሆኑትና የሚሞቱት ለምንድን ነው?

የመጀመሪያዎቹ ወላጆቻችን የሆኑት አዳምና ሔዋን በአምላክ ላይ ኃጢአት በመሥራታቸው ምክንያት ሞተዋል። (ዘፍጥረት 3:17-19) አምላክ “የሕይወት ምንጭ” በመሆኑ በእሱ ላይ ማመፅ ሞት ማስከተሉ ሳይታለም የተፈታ ነው።​—መዝሙር 36:9፤ ዘፍጥረት 2:17

አዳም የነበረበትን ኃጢአት ለዘሮቹ በሙሉ አስተላልፏል። መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦ “በአንድ ሰው አማካኝነት ኃጢአት ወደ ዓለም ገባ፤ በኃጢአትም ምክንያት ሞት መጣ፤ ሁሉም ኃጢአት ስለሠሩም ሞት ለሰው ሁሉ ተዳረሰ።” (ሮም 5:12) ሁሉም ሰዎች የሚሞቱት ኃጢአተኞች በመሆናቸው ነው።​—ሮም 3:23

ሞት የሚወገደው እንዴት ነው?

አምላክ ‘ሞትን ለዘላለም የሚውጥበት’ ጊዜ እንደሚመጣ ቃል ገብቷል። (ኢሳይያስ 25:8) ሞትን ለማስወገድ ግን መጀመሪያ ምንጩን ማለትም ኃጢአትን ማጥፋት ያስፈልገዋል። አምላክ ይህን የሚያደርገው ‘የዓለምን ኃጢአት በሚያስወግደው’ በኢየሱስ ክርስቶስ አማካኝነት ነው።​—ዮሐንስ 1:29፤ 1 ዮሐንስ 1:7

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ