የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • w15 9/1 ገጽ 5
  • የይሖዋ ምሥክሮች ምን ብለው ያምናሉ?

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

  • የይሖዋ ምሥክሮች ምን ብለው ያምናሉ?
  • የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2015
  • ተመሳሳይ ሐሳብ ያለው ርዕስ
  • የይሖዋ ምሥክሮች ምን ብለው ያምናሉ?
    የይሖዋ ምሥክሮች ምን ብለው ያምናሉ?
  • የይሖዋ ምሥክሮች ምን ብለው ያምናሉ?
    የይሖዋ ምሥክሮች ምን ብለው ያምናሉ?
  • የይሖዋ ምሥክሮች
    ከቅዱሳን ጽሑፎች እየጠቀሱ ማመራመር
  • የምንሰብከው ለምንድን ነው?
    የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2015
ለተጨማሪ መረጃ
የይሖዋን መንግሥት የሚያስታውቅ መጠበቂያ ግንብ—2015
w15 9/1 ገጽ 5
የይሖዋ ምሥክሮች የሆኑ ባልና ሚስት ልጆቻቸውን መጽሐፍ ቅዱስ ሲያስጠኑ

የሽፋኑ ርዕሰ ጉዳይ | የይሖዋ ምሥክሮች እነማን ናቸው?

የይሖዋ ምሥክሮች ምን ብለው ያምናሉ?

የይሖዋ ምሥክሮች ‘ቅዱሳን መጻሕፍት ሁሉ በአምላክ መንፈስ መሪነት የተጻፉና ጠቃሚ’ እንደሆኑ ያምናሉ። (2 ጢሞቴዎስ 3:16) መጽሐፍ ቅዱስ፣ ስለ ፈጣሪ ለመማርና ትርጉም ያለው ሕይወት ለመኖር እንደሚረዳ ስለምናምን የሕይወታችን መመሪያ ነው።

መጽሐፍ ቅዱስ “ስምህ ይሖዋ የሆነው አንተ፣ አዎ፣ አንተ ብቻ በመላው ምድር ላይ ልዑል እንደሆንክ ሰዎች ይወቁ” ይላል። (መዝሙር 83:18) በመሆኑም ይሖዋ አምላክን ብቻ የምናመልክ ሲሆን የእሱ ምሥክሮች በመሆናችን የግል ስሙን ለማሳወቅ ጥረት እናደርጋለን።—ኢሳይያስ 43:10-12

ክርስቲያኖች እንደመሆናችን መጠን ደግሞ “የአምላክ ልጅ”a የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድር እንደመጣና መሲሕ ሆኖ እንደተሾመ እናምናለን። (ዮሐንስ 1:34, 41፤ 4:25, 26) ኢየሱስ ከሞት ከተነሳ በኋላ ወደ ሰማይ ሄዷል። (1 ቆሮንቶስ 15:3, 4) ከጊዜ በኋላ ደግሞ የአምላክ መንግሥት ንጉሥ ሆኗል። (ራእይ 11:15) ይህ መንግሥት ምድርን ዳግመኛ ገነት የሚያደርግ በተጨባጭ ያለ መስተዳድር ነው። (ዳንኤል 2:44) መጽሐፍ ቅዱስ “የዋሆች ግን ምድርን ይወርሳሉ፤ በብዙ ሰላምም እጅግ ደስ ይላቸዋል” ይላል።—መዝሙር 37:11, 29

“የይሖዋ ምሥክሮች መጽሐፍ ቅዱስን ሲያነቡ አምላክ እያነጋገራቸው እንዳለ ይሰማቸዋል። በሕይወታቸው ውስጥ ችግር ሲያጋጥማቸው መፍትሔውን ከአምላክ ቃል ለማግኘት ጥረት ያደርጋሉ። . . . ለእነሱ የአምላክ ቃል አሁንም ሕያው ነው።”—የካቶሊክ ቄስ ቤንጃሚን ቼራያዝ፣ ሚዩንስተርላንደሽ ፎልክስጻይቱንግ ጋዜጣ፣ ጀርመን

የይሖዋ ምሥክሮች፣ የመጽሐፍ ቅዱስ መመሪያዎች በዛሬው ጊዜ እንኳ ሳይቀር ለሰዎች ጠቃሚ እንደሆኑ ያምናሉ። (ኢሳይያስ 48:17, 18) ስለዚህ እነዚህን መመሪያዎች በጥብቅ እንከተላለን። ለምሳሌ ያህል፣ መጽሐፍ ቅዱስ አእምሯችንንና አካላችንን ከሚበክሉ ልማዶች እንድንርቅ ስለሚያስጠነቅቀን ሲጋራ አናጨስም ወይም በአደንዛዥ መድኃኒቶች አላግባብ አንጠቀምም። (2 ቆሮንቶስ 7:1) በተጨማሪም እንደ ስካር፣ ስርቆትና የፆታ ብልግና ካሉ መጽሐፍ ቅዱስ በቀጥታ ከሚያወግዛቸው ልማዶች እንርቃለን።—1 ቆሮንቶስ 6:9-11

a መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስን “የአምላክ አንድያ ልጅ” በማለትም ይጠራዋል፤ እንዲህ የተባለው በይሖዋ አምላክ በቀጥታ የተፈጠረው የመጀመሪያው ፍጡር እሱ ብቻ ስለሆነ ነው።—ዮሐንስ 3:18፤ ቆላስይስ 1:13-15

አንድ ትንሽ ልጅ የተሰጠውን ስጦታ ሲከፍት ወላጆቹ በፈገግታ ሲያዩት

www.pr2711.com ላይ ስለ እኛ > ብዙ ጊዜ የሚነሱ ጥያቄዎች በሚለው ሥር በዓላትን የማናከብርበትን ወይም ለሕክምና ደም የማንወስድበትን ምክንያት ጨምሮ ስለምናምንባቸው ነገሮች ማወቅ ትችላለህ።

    አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
    ውጣ
    ግባ
    • አማርኛ
    • አጋራ
    • የግል ምርጫዎች
    • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
    • የአጠቃቀም ውል
    • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
    • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
    • JW.ORG
    • ግባ
    አጋራ