መዝሙር
ወደ ላይ የመውጣት መዝሙር።
3 “ወደ ድንኳኔ፣ ወደ ቤቴ አልገባም።+
ወደ መኝታዬ፣ ወደ አልጋዬ አልወጣም፤
4 ዓይኖቼ እንዲያንቀላፉ፣
ሽፋሽፍቶቼም እንዲያሸልቡ አልፈቅድም፤
5 ይህም ለይሖዋ ስፍራ፣
ኃያል ለሆነው የያዕቆብ አምላክም ያማረ መኖሪያ እስከማገኝ ድረስ ነው።”+
9 ካህናትህ ጽድቅን ይልበሱ፤
ታማኝ አገልጋዮችህም እልል ይበሉ።
10 ለአገልጋይህ ለዳዊት ስትል፣
የቀባኸውን ሰው ገሸሽ አታድርግ።+
11 ይሖዋ ለዳዊት ምሏል፤
የገባውን ቃል ፈጽሞ አያጥፍም፦
14 “ይህች ለዘላለም ማረፊያ ስፍራዬ ነች፤
በእሷ እኖራለሁ፤+ ይህ ምኞቴ ነውና።
15 የተትረፈረፈ የምግብ አቅርቦት እንዲኖራት በማድረግ እባርካታለሁ፤
ድሆቿን እህል አጠግባለሁ።+
17 በዚያ የዳዊትን ብርታት እጨምራለሁ።*
ለቀባሁት አገልጋዬ መብራት አዘጋጅቻለሁ።+