የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ዘፀአት 18
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ዘፀአት የመጽሐፉ ይዘት

      • ዮቶርና ሲፓራ ወደ ሙሴ መጡ (1-12)

      • ሙሴ ፈራጆችን እንዲሾም ዮቶር መከረው (13-27)

ዘፀአት 18:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፀ 2:16, 21፤ 3:1
  • +ኢያሱ 2:9, 10፤ 9:3, 9

ዘፀአት 18:3

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    “በዚያ የሚኖር የባዕድ አገር ሰው” የሚል ትርጉም አለው።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሥራ 7:29
  • +ዘፀ 2:22

ዘፀአት 18:4

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    “አምላኬ ረዳት ነው” የሚል ትርጉም አለው።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፀ 2:15

ዘፀአት 18:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፀ 19:2፤ 1ነገ 19:8, 9

ዘፀአት 18:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፀ 4:18፤ ዘኁ 10:29

ዘፀአት 18:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፀ 7:3፤ 14:27, 28፤ ዘዳ 4:34
  • +ዘፀ 15:22፤ 16:3

ዘፀአት 18:11

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፀ 15:11፤ መዝ 95:3፤ 97:9

ዘፀአት 18:16

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 4:5፤ 5:1

ዘፀአት 18:19

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢያሱ 1:5, 17
  • +ዘፀ 20:19
  • +ዘኁ 27:1-5

ዘፀአት 18:20

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 7:11

ዘፀአት 18:21

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 11:16, 17፤ ዘዳ 1:13፤ ሥራ 6:3
  • +ዘፀ 23:8፤ 1ጢሞ 3:2, 3፤ ቲቶ 1:7፤ 1ጴጥ 5:2
  • +ዘዳ 1:15፤ ሥራ 14:23

ዘፀአት 18:22

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “እነሱም በማንኛውም ጊዜ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘሌ 24:10, 11፤ ዘኁ 15:32, 33፤ ዘዳ 1:17
  • +ዘኁ 11:17

ዘፀአት 18:26

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሥራ 15:2

ዘፀአት 18:27

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 10:29

ተዛማጅ ሐሳብ

ዘፀ. 18:1ዘፀ 2:16, 21፤ 3:1
ዘፀ. 18:1ኢያሱ 2:9, 10፤ 9:3, 9
ዘፀ. 18:3ሥራ 7:29
ዘፀ. 18:3ዘፀ 2:22
ዘፀ. 18:4ዘፀ 2:15
ዘፀ. 18:5ዘፀ 19:2፤ 1ነገ 19:8, 9
ዘፀ. 18:6ዘፀ 4:18፤ ዘኁ 10:29
ዘፀ. 18:8ዘፀ 7:3፤ 14:27, 28፤ ዘዳ 4:34
ዘፀ. 18:8ዘፀ 15:22፤ 16:3
ዘፀ. 18:11ዘፀ 15:11፤ መዝ 95:3፤ 97:9
ዘፀ. 18:16ዘዳ 4:5፤ 5:1
ዘፀ. 18:19ኢያሱ 1:5, 17
ዘፀ. 18:19ዘፀ 20:19
ዘፀ. 18:19ዘኁ 27:1-5
ዘፀ. 18:20ዘዳ 7:11
ዘፀ. 18:21ዘኁ 11:16, 17፤ ዘዳ 1:13፤ ሥራ 6:3
ዘፀ. 18:21ዘፀ 23:8፤ 1ጢሞ 3:2, 3፤ ቲቶ 1:7፤ 1ጴጥ 5:2
ዘፀ. 18:21ዘዳ 1:15፤ ሥራ 14:23
ዘፀ. 18:22ዘሌ 24:10, 11፤ ዘኁ 15:32, 33፤ ዘዳ 1:17
ዘፀ. 18:22ዘኁ 11:17
ዘፀ. 18:26ሥራ 15:2
ዘፀ. 18:27ዘኁ 10:29
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
  • 26
  • 27
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ዘፀአት 18:1-27

ዘፀአት

18 የምድያም ካህን የሆነው የሙሴ አማት ዮቶር+ አምላክ ለሙሴና ለሕዝቡ ለእስራኤል ያደረገውን ነገር ሁሉ ይኸውም ይሖዋ እስራኤልን ከግብፅ እንዴት እንዳወጣ ሰማ።+ 2 የሙሴ አማት ዮቶር የሙሴ ሚስት ሲፓራ ወደ እሱ ተመልሳ በተላከች ጊዜ እሷንና 3 ሁለቱን ወንዶች ልጆቿን+ ይዞ ተነሳ። ሙሴ “በባዕድ አገር የምኖር የባዕድ አገር ሰው ሆንኩ” ብሎ ስለነበር የአንደኛው ልጅ ስም ጌርሳም*+ ነበር፤ 4 እንዲሁም ሙሴ “ከፈርዖን ሰይፍ+ ያዳነኝ የአባቴ አምላክ ረዳቴ ነው” ብሎ ስለነበር የሌላኛው ልጁ ስም ኤሊዔዘር* ነበር።

5 በመሆኑም የሙሴ አማት ዮቶር ከሙሴ ሚስትና ወንዶች ልጆች ጋር በመሆን የእውነተኛው አምላክ ተራራ+ በሚገኝበት ምድረ በዳ ሰፍሮ ወደነበረው ወደ ሙሴ መጣ። 6 ከዚያም ዮቶር “እኔ አማትህ ዮቶር፣+ ከሚስትህና ከሁለቱ ወንዶች ልጆቿ ጋር ወደ አንተ እየመጣሁ ነው” የሚል መልእክት ወደ ሙሴ ላከ። 7 ሙሴም ወዲያውኑ አማቱን ሊቀበለው ወጣ፤ እሱም ሰገደለት፤ ከዚያም ሳመው። እርስ በርሳቸውም ስለ ደህንነታቸው ተጠያየቁ፤ በኋላም ወደ ድንኳኑ ገቡ።

8 ሙሴም ይሖዋ ለእስራኤል ሲል በፈርዖንና በግብፅ ላይ ያደረገውን ሁሉ+ እንዲሁም በጉዟቸው ያጋጠሟቸውን አስቸጋሪ ሁኔታዎችና+ ይሖዋ እንዴት እንዳዳናቸው ለአማቱ ተረከለት። 9 ዮቶርም ይሖዋ እስራኤልን ከግብፅ እጅ በማዳን ለእነሱ ሲል ባደረገላቸው መልካም ነገሮች ሁሉ ተደሰተ። 10 ከዚያም ዮቶር እንዲህ አለ፦ “ከግብፅና ከፈርዖን እጅ ያዳናችሁ እንዲሁም ሕዝቡን ከግብፅ እጅ ነፃ ያወጣው ይሖዋ ይወደስ። 11 ይሖዋ በሕዝቡ ላይ የእብሪት ድርጊት በፈጸሙ ሰዎች ላይ እንዲህ ያለ እርምጃ በመውሰዱ ከሌሎች አማልክት ሁሉ እንደሚበልጥ+ አሁን አውቄአለሁ።” 12 ከዚያም የሙሴ አማት ዮቶር የሚቃጠል መባና መሥዋዕቶችን ለአምላክ አመጣ፤ አሮንና የእስራኤል ሽማግሌዎች በሙሉ ከሙሴ አማት ጋር በእውነተኛው አምላክ ፊት ምግብ ለመብላት መጡ።

13 በማግስቱም ሙሴ እንደተለመደው ሕዝቡን በዳኝነት ለማገልገል ተቀመጠ፤ ሕዝቡም ከጠዋት አንስቶ እስከ ማታ ድረስ እየመጣ በሙሴ ፊት ይቆም ነበር። 14 የሙሴ አማትም ሙሴ ለሕዝቡ የሚያደርገውን ሁሉ ባየ ጊዜ “ይህ ለሕዝቡ እያደረግክ ያለኸው ነገር ምንድን ነው? አንተ ብቻህን ለመዳኘት የምትቀመጠውና ይህ ሁሉ ሕዝብ ከጠዋት እስከ ማታ ድረስ ፊትህ የሚቆመው ለምንድን ነው?” አለው። 15 ሙሴም አማቱን እንዲህ አለው፦ “ምክንያቱም ሕዝቡ አምላክን ለመጠየቅ ያለማቋረጥ ወደ እኔ ይመጣል። 16 አንድ ጉዳይ በሚነሳበት ጊዜ ጉዳዩ ወደ እኔ ይቀርባል፤ እኔ ደግሞ ባለጉዳዮቹን እዳኛለሁ፤ እንዲሁም የእውነተኛውን አምላክ ውሳኔዎችና ሕጎች አሳውቃለሁ።”+

17 በዚህ ጊዜ የሙሴ አማት እንዲህ አለው፦ “እያደረግክ ያለኸው ነገር መልካም አይደለም። 18 ይህ ሥራ ለአንተ ከባድ ሸክም ስለሚሆን አንተም ሆንክ ከአንተ ጋር ያለው ይህ ሕዝብ መድከማችሁ አይቀርም፤ ደግሞም ብቻህን ልትሸከመው አትችልም። 19 እንግዲህ አሁን የምልህን ስማ። አንድ ነገር ልምከርህ፤ አምላክም ከአንተ ጋር ይሆናል።+ አንተ በእውነተኛው አምላክ ፊት የሕዝቡ ተወካይ ሆነህ ታገለግላለህ፤+ ጉዳያቸውንም ወደ እውነተኛው አምላክ ታቀርባለህ።+ 20 ሥርዓቶቹና ሕጎቹ ምን እንደሆኑ በመንገር ማሳሰቢያ ትሰጣቸዋለህ፤+ እንዲሁም የሚሄዱበትን መንገድና የሚያከናውኑትን ነገር ታሳውቃቸዋለህ። 21 ሆኖም ከመላው ሕዝብ መካከል አምላክን የሚፈሩትንና ብቃት ያላቸውን+ እንዲሁም አግባብ ያልሆነ ጥቅም ለማግኘት የማይፈልጉትንና እምነት የሚጣልባቸውን ሰዎች+ ምረጥ፤ እነዚህንም የሺህ አለቆች፣ የመቶ አለቆች፣ የሃምሳ አለቆችና የአሥር አለቆች አድርገህ በሕዝቡ ላይ ሹማቸው።+ 22 እነሱም የተለያዩ ጉዳዮች በሚነሱበት ጊዜ* ሕዝቡን ይዳኙ፤ ከበድ ያሉ ጉዳዮች ሲያጋጥሟቸው ወደ አንተ ያምጡ፤+ ቀለል ያሉ ጉዳዮችን ግን ራሳቸው ይዳኙ። ሸክሙን እንዲጋሩህ በማድረግ በአንተ ላይ ያለውን ጫና አቅልል።+ 23 ይህን ነገር ከአምላክ እንደተቀበልከው ትእዛዝ አድርገህ ብትፈጽም ውጥረቱ ይቀንስልሃል፤ እያንዳንዱም ሰው ተደስቶ ወደ ቤቱ ይሄዳል።”

24 ሙሴም ወዲያውኑ አማቱን በመስማት ያለውን ሁሉ አደረገ። 25 ሙሴም ከመላው እስራኤል ብቃት ያላቸውን ወንዶች መርጦ የሺህ አለቆች፣ የመቶ አለቆች፣ የሃምሳ አለቆችና የአሥር አለቆች አድርጎ በሕዝቡ ላይ ሾማቸው። 26 በመሆኑም እነዚህ ሰዎች የተለያዩ ጉዳዮች በሚነሱበት ጊዜ ሕዝቡን ይዳኙ ነበር። ከበድ ያለ ጉዳይ ሲያጋጥማቸው ወደ ሙሴ ያመጡ+ የነበረ ሲሆን ቀለል ያሉ ጉዳዮችን ግን ራሳቸው ይዳኙ ነበር። 27 ከዚያም ሙሴ አማቱን ሸኘው፤+ እሱም ወደ አገሩ ሄደ።

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ