ምሳሌ
4 ይሖዋ ማንኛውንም ነገር ያዘጋጀው ለራሱ ዓላማ ነው፤
ክፉውም ሰው እንኳ በመዓት ቀን እንዲጠፋ ያደርጋል።+
5 ይሖዋ ኩሩ ልብ ያለውን ሁሉ ይጸየፋል።+
እንዲህ ያለው ሰው ሳይቀጣ እንደማይቀር እርግጠኛ ሁን።
7 ይሖዋ በሰው አካሄድ ደስ በሚሰኝበት ጊዜ
ጠላቶቹ እንኳ ሳይቀሩ ከሰውየው ጋር ሰላም እንዲኖራቸው ያደርጋል።+
8 አግባብ ባልሆነ መንገድ ከሚገኝ ብዙ ገቢ ይልቅ
በጽድቅ የሚገኝ ጥቂት ነገር ይሻላል።+
9 ሰው በልቡ መንገዱን ያቅዳል፤
ይሖዋ ግን አካሄዱን ይመራለታል።+
11 ትክክለኛ መለኪያና ሚዛን ከይሖዋ ናቸው፤
በከረጢት ውስጥ ያሉት መለኪያዎች ሁሉ የእሱ ሥራ ናቸው።+
13 ነገሥታት የጽድቅ ንግግር ደስ ያሰኛቸዋል።
ሐቁን የሚናገር ሰው ይወዳሉ።+
15 የንጉሥ ፊት ሲፈካ ሰው በደስታ ይኖራል፤
ሞገሱም ዝናብ እንዳዘለ የበልግ ደመና ነው።+
16 ጥበብን ማግኘት ወርቅ ከማግኘት ምንኛ የተሻለ ነው!+
ማስተዋልን ማግኘትም ብር ከማግኘት ይመረጣል።+
17 ቅኖች ከክፋት ጎዳና ይርቃሉ።
18 ኩራት ጥፋትን፣
የትዕቢት መንፈስም ውድቀትን ይቀድማል።+
20 አንድን ነገር ጠለቅ ብሎ የሚያስተውል ሰው ስኬታማ ይሆናል፤*
በይሖዋ የሚታመንም ደስተኛ ነው።
22 ጥልቅ ማስተዋል ለባለቤቱ የሕይወት ምንጭ ነው፤
ሞኞች ግን በገዛ ሞኝነታቸው ይቀጣሉ።
23 የጥበበኛ ሰው ልብ፣ አንደበቱ ጥልቅ ማስተዋል እንዲኖረው ያደርጋል፤+
ለንግግሩም የማሳመን ችሎታ ይጨምርለታል።
25 ለሰው ትክክለኛ መስሎ የሚታይ መንገድ አለ፤
በመጨረሻ ግን ወደ ሞት ይመራል።+
29 ዓመፀኛ ሰው ባልንጀራውን ክፉ ነገር እንዲሠራ ያግባባዋል፤
ወደተሳሳተ መንገድም ይመራዋል።
30 በዓይኑ እየጠቀሰ ተንኮል ይሸርባል።
ከንፈሮቹን ነክሶ ሸር ይሠራል።