የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኢሳይያስ 1
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ኢሳይያስ የመጽሐፉ ይዘት

      • አንድ አባትና ዓመፀኛ ልጆቹ (1-9)

      • ይሖዋ ለታይታ ተብሎ የሚቀርብን አምልኮ ይጠላል (10-17)

      • “የተፈጠረውን ችግር ተወያይተን እንፍታ” (18-20)

      • ጽዮን ዳግመኛ የታመነች ከተማ ትሆናለች (21-31)

ኢሳይያስ 1:1

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    “የይሖዋ ማዳን” ማለት ነው።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ማቴ 1:9
  • +2ዜና 26:22፤ ኢሳ 6:1
  • +2ዜና 27:1, 2
  • +2ዜና 28:1
  • +2ዜና 29:1, 2፤ 32:20
  • +2ዜና 32:32

ኢሳይያስ 1:2

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 50:4
  • +ዘዳ 1:31
  • +ዘዳ 4:25, 26፤ ሕዝ 20:8

ኢሳይያስ 1:3

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ጌታውን።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሆሴዕ 4:6

ኢሳይያስ 1:4

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዳን 9:11
  • +ዘዳ 31:16፤ ኤር 2:5

ኢሳይያስ 1:5

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 5:3
  • +ነህ 9:34, 35፤ ዳን 9:8

ኢሳይያስ 1:6

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “አልፈረጠም።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሉቃስ 10:34

ኢሳይያስ 1:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 28:33, 63
  • +2ነገ 18:11

ኢሳይያስ 1:8

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ዳስ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ነገ 18:13, 14፤ ኢሳ 8:7, 8

ኢሳይያስ 1:9

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 19:24, 25፤ ዘዳ 29:22, 23፤ ሮም 9:29

ኢሳይያስ 1:10

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ገዢዎች።”

  • *

    ወይም “መመሪያ፤ ትምህርት።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፍ 13:13፤ ኢሳ 3:8, 9
  • +ዘዳ 32:32፤ ይሁዳ 7

ኢሳይያስ 1:11

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +1ሳሙ 15:22፤ ምሳሌ 15:8፤ ሆሴዕ 6:6፤ ሚክ 6:7
  • +ዘፀ 29:38
  • +ዘሌ 3:14-16
  • +ዘሌ 4:18, 21
  • +ዘሌ 16:5
  • +ዘሌ 17:11

ኢሳይያስ 1:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 16:16
  • +መክ 5:1፤ ሚል 1:8

ኢሳይያስ 1:13

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ምሳሌ 21:27፤ ሕዝ 8:11, 12
  • +ዘኁ 28:11
  • +ዘፀ 31:13
  • +ዘሌ 23:2
  • +ዘሌ 19:26

ኢሳይያስ 1:14

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሴ ጠልታለች።”

ኢሳይያስ 1:15

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ምሳሌ 15:29
  • +ማቴ 6:7
  • +ምሳሌ 28:9፤ ኢሳ 59:2፤ ሰቆ 3:44
  • +ሚክ 3:2-4

ኢሳይያስ 1:16

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 4:14
  • +ኢሳ 55:7

ኢሳይያስ 1:17

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ወላጅ አልባ የሆነውን ልጅ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሚክ 6:8
  • +ዘዳ 10:18፤ ኤር 22:3

ኢሳይያስ 1:18

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሚክ 6:2፤ ያዕ 4:8
  • +መዝ 51:7፤ ኢሳ 44:22፤ ሚክ 7:19

ኢሳይያስ 1:19

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 28:1, 2፤ ኢዩ 2:19

ኢሳይያስ 1:20

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘሌ 26:33፤ ምሳሌ 29:1

ኢሳይያስ 1:21

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 48:2
  • +ኤር 2:20
  • +2ሳሙ 8:15፤ 1ነገ 3:28
  • +2ዜና 19:9, 10
  • +ሚክ 3:1-3፤ ሉቃስ 13:34

ኢሳይያስ 1:22

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ከስንዴ የሚዘጋጀው ጠላሽ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሕዝ 22:18

ኢሳይያስ 1:23

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ወላጅ አልባ የሆኑ ልጆች ፍትሕ እንዲያገኙ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 3:14፤ ሚክ 3:9-11
  • +ዘፀ 23:8
  • +ዘፀ 22:22፤ ኤር 5:28

ኢሳይያስ 1:24

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሕዝ 5:13

ኢሳይያስ 1:25

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 6:29, 30፤ 9:7፤ ሚል 3:3

ኢሳይያስ 1:26

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘኁ 12:3፤ 1ሳሙ 12:1, 3፤ ኢሳ 32:1፤ ሕዝ 34:23
  • +ኢሳ 62:1

ኢሳይያስ 1:27

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 31:11

ኢሳይያስ 1:28

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሕዝ 20:38
  • +1ነገ 9:6, 7

ኢሳይያስ 1:29

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ከጣዖት አምልኮ ጋር ግንኙነት ያላቸውን ዛፎችና የአትክልት ቦታዎች የሚያመለክት ይመስላል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሕዝ 6:13
  • +ኢሳ 65:3፤ 66:17

ኢሳይያስ 1:30

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 17:5, 6

ኢሳይያስ 1:31

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ተቀጣጣይ የሆነ ገመድ መሰል ቃጫ።

ተዛማጅ ሐሳብ

ኢሳ. 1:1ማቴ 1:9
ኢሳ. 1:12ዜና 26:22፤ ኢሳ 6:1
ኢሳ. 1:12ዜና 27:1, 2
ኢሳ. 1:12ዜና 28:1
ኢሳ. 1:12ዜና 29:1, 2፤ 32:20
ኢሳ. 1:12ዜና 32:32
ኢሳ. 1:2መዝ 50:4
ኢሳ. 1:2ዘዳ 1:31
ኢሳ. 1:2ዘዳ 4:25, 26፤ ሕዝ 20:8
ኢሳ. 1:3ሆሴዕ 4:6
ኢሳ. 1:4ዳን 9:11
ኢሳ. 1:4ዘዳ 31:16፤ ኤር 2:5
ኢሳ. 1:5ኤር 5:3
ኢሳ. 1:5ነህ 9:34, 35፤ ዳን 9:8
ኢሳ. 1:6ሉቃስ 10:34
ኢሳ. 1:7ዘዳ 28:33, 63
ኢሳ. 1:72ነገ 18:11
ኢሳ. 1:82ነገ 18:13, 14፤ ኢሳ 8:7, 8
ኢሳ. 1:9ዘፍ 19:24, 25፤ ዘዳ 29:22, 23፤ ሮም 9:29
ኢሳ. 1:10ዘፍ 13:13፤ ኢሳ 3:8, 9
ኢሳ. 1:10ዘዳ 32:32፤ ይሁዳ 7
ኢሳ. 1:111ሳሙ 15:22፤ ምሳሌ 15:8፤ ሆሴዕ 6:6፤ ሚክ 6:7
ኢሳ. 1:11ዘፀ 29:38
ኢሳ. 1:11ዘሌ 3:14-16
ኢሳ. 1:11ዘሌ 4:18, 21
ኢሳ. 1:11ዘሌ 16:5
ኢሳ. 1:11ዘሌ 17:11
ኢሳ. 1:12ዘዳ 16:16
ኢሳ. 1:12መክ 5:1፤ ሚል 1:8
ኢሳ. 1:13ምሳሌ 21:27፤ ሕዝ 8:11, 12
ኢሳ. 1:13ዘኁ 28:11
ኢሳ. 1:13ዘፀ 31:13
ኢሳ. 1:13ዘሌ 23:2
ኢሳ. 1:13ዘሌ 19:26
ኢሳ. 1:15ምሳሌ 15:29
ኢሳ. 1:15ማቴ 6:7
ኢሳ. 1:15ምሳሌ 28:9፤ ኢሳ 59:2፤ ሰቆ 3:44
ኢሳ. 1:15ሚክ 3:2-4
ኢሳ. 1:16ኤር 4:14
ኢሳ. 1:16ኢሳ 55:7
ኢሳ. 1:17ሚክ 6:8
ኢሳ. 1:17ዘዳ 10:18፤ ኤር 22:3
ኢሳ. 1:18ሚክ 6:2፤ ያዕ 4:8
ኢሳ. 1:18መዝ 51:7፤ ኢሳ 44:22፤ ሚክ 7:19
ኢሳ. 1:19ዘዳ 28:1, 2፤ ኢዩ 2:19
ኢሳ. 1:20ዘሌ 26:33፤ ምሳሌ 29:1
ኢሳ. 1:21መዝ 48:2
ኢሳ. 1:21ኤር 2:20
ኢሳ. 1:212ሳሙ 8:15፤ 1ነገ 3:28
ኢሳ. 1:212ዜና 19:9, 10
ኢሳ. 1:21ሚክ 3:1-3፤ ሉቃስ 13:34
ኢሳ. 1:22ሕዝ 22:18
ኢሳ. 1:23ኢሳ 3:14፤ ሚክ 3:9-11
ኢሳ. 1:23ዘፀ 23:8
ኢሳ. 1:23ዘፀ 22:22፤ ኤር 5:28
ኢሳ. 1:24ሕዝ 5:13
ኢሳ. 1:25ኤር 6:29, 30፤ 9:7፤ ሚል 3:3
ኢሳ. 1:26ዘኁ 12:3፤ 1ሳሙ 12:1, 3፤ ኢሳ 32:1፤ ሕዝ 34:23
ኢሳ. 1:26ኢሳ 62:1
ኢሳ. 1:27ኤር 31:11
ኢሳ. 1:28ሕዝ 20:38
ኢሳ. 1:281ነገ 9:6, 7
ኢሳ. 1:29ሕዝ 6:13
ኢሳ. 1:29ኢሳ 65:3፤ 66:17
ኢሳ. 1:30ኤር 17:5, 6
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
  • 26
  • 27
  • 28
  • 29
  • 30
  • 31
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ኢሳይያስ 1:1-31

ኢሳይያስ

1 የይሁዳ ነገሥታት+ በሆኑት በዖዝያ፣+ በኢዮዓታም፣+ በአካዝና+ በሕዝቅያስ+ ዘመን የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ* ስለ ይሁዳና ስለ ኢየሩሳሌም ያየው ራእይ፦+

 2 ሰማያት ሆይ፣ ስሙ፤ ምድር ሆይ፣ አድምጪ፤+

ይሖዋ እንዲህ ሲል ተናግሯልና፦

“ወንዶች ልጆችን ተንከባክቤ አሳደግኩ፤+

እነሱ ግን በእኔ ላይ ዓመፁ።+

 3 በሬ ጌታውን፣

አህያም የባለቤቱን ጋጣ በሚገባ ያውቃል፤

እስራኤል ግን እኔን* አላወቀም፤+

የገዛ ሕዝቤም አላስተዋለም።”

 4 ኃጢአተኛ የሆነው ብሔር፣+

ከባድ በደል የተጫነው ሕዝብ፣

የክፉዎች ዘር፣ ብልሹ የሆኑ ልጆች ወዮላቸው!

እነሱ ይሖዋን ትተዋል፤+

የእስራኤልን ቅዱስ አቃለዋል፤

ጀርባቸውን ሰጥተውታል።

 5 በዓመፅ ላይ ዓመፅ የምትጨምሩት፣ አሁን ደግሞ ምናችሁ ላይ መመታት ፈልጋችሁ ነው?+

መላው ራስ ታሟል፤

መላው ልብም በበሽታ ተይዟል።+

 6 ከእግር ጥፍር አንስቶ እስከ ራስ ፀጉር ድረስ አንድም ጤነኛ የአካል ክፍል የለም።

በቁስልና በሰምበር ተሞልቷል፤ እንዲሁም ተተልትሏል፤

ቁስሉ አልታከመም* ወይም አልታሰረም አሊያም በዘይት አለዘበም።+

 7 ምድራችሁ ባድማ ሆኗል።

ከተሞቻችሁ በእሳት ጋይተዋል።

የባዕድ አገር ሰዎች ዓይናችሁ እያየ ምድራችሁን ይውጣሉ።+

ባዕዳን እንዳወደሙት ጠፍ መሬት ሆኗል።+

 8 የጽዮን ሴት ልጅ በወይን እርሻ ውስጥ እንዳለ መጠለያ፣*

በኪያር የእርሻ ቦታ እንዳለ ጎጆ፣

እንደተከበበችም ከተማ ተትታለች።+

 9 የሠራዊት ጌታ ይሖዋ ጥቂት ሰዎች ከጥፋት እንዲተርፉልን ባያደርግ ኖሮ

እንደ ሰዶም በሆንን፣

ገሞራንም በመሰልን ነበር።+

10 እናንተ የሰዶም+ አምባገነኖች፣* የይሖዋን ቃል ስሙ።

እናንተ የገሞራ+ ሰዎች፣ የአምላካችንን ሕግ* አዳምጡ።

11 “የመሥዋዕታችሁ ብዛት ለእኔ ምን ይጠቅመኛል?”+ ይላል ይሖዋ።

“የሚቃጠሉ የአውራ በግ መባዎችና+ የደለቡ እንስሳት ስብ+ በቅቶኛል፤

በወይፈኖች፣+ በበግ ጠቦቶችና በፍየሎች+ ደም+ ደስ አልሰኝም።

12 በፊቴ ለመቅረብ የምትመጡት፣+

ይህን እንድታደርጉ፣

የቤተ መቅደሴን ግቢ እንድትረግጡ ማን ጠይቋችሁ ነው?+

13 ከንቱ የሆኑትን የእህል መባዎች ከዚህ በኋላ አታምጡ።

ዕጣናችሁ በፊቴ አስጸያፊ ነው።+

የአዲስ ጨረቃ+ በዓልንና ሰንበትን+ ታከብራላችሁ፤ ስብሰባም+ ትጠራላችሁ።

በአንድ በኩል የተቀደሱ ጉባኤዎችን እያከበራችሁ በሌላ በኩል የምትፈጽሙትን አስማታዊ ድርጊት+ መታገሥ አልችልም።

14 የአዲስ ጨረቃ በዓሎቻችሁንና ሌሎች በዓሎቻችሁን ጠልቻለሁ።*

ለእኔ ሸክም ሆነውብኛል፤

እነሱንም ከመሸከሜ የተነሳ ዝያለሁ።

15 እጆቻችሁን ስትዘረጉ

ዓይኖቼን ከእናንተ እሰውራለሁ።+

ጸሎት ብታበዙም እንኳ+

አልሰማችሁም፤+

እጆቻችሁ በደም ተሞልተዋል።+

16 ታጠቡ፤ ራሳችሁንም አንጹ፤+

ክፉ ሥራችሁን ከፊቴ አስወግዱ፤

መጥፎ ድርጊት መፈጸማችሁን አቁሙ።+

17 መልካም ማድረግን ተማሩ፤ ፍትሕን ፈልጉ፤+

ጨቋኙ እንዲታረም አድርጉ፤

አባት የሌለውን ልጅ* መብት አስከብሩ፤

ለመበለቲቱም ተሟገቱ።”+

18 “ኑና በመካከላችን የተፈጠረውን ችግር ተወያይተን እንፍታ” ይላል ይሖዋ።+

“ኃጢአታችሁ እንደ ደም ቢቀላ

እንደ በረዶ ይነጣል፤+

እንደ ደማቅ ቀይ ጨርቅ ቢቀላም

እንደ ነጭ የሱፍ ጨርቅ ይሆናል።

19 እሺ ብትሉና ብትታዘዙ

የምድሪቱን መልካም ፍሬ ትበላላችሁ።+

20 እንቢ ብትሉና ብታምፁ ግን

ሰይፍ ይበላችኋል፤+

የይሖዋ አፍ ይህን ተናግሯልና።”

21 ታማኝ የነበረችው ከተማ+ እንዴት ዝሙት አዳሪ ሆነች!+

ፍትሕ የሞላባትና+

ጽድቅ የሰፈነባት ነበረች፤+

አሁን ግን የነፍሰ ገዳዮች ጎሬ ሆናለች።+

22 ብርሽ እንደ ዝቃጭ ሆኗል፤+

መጠጥሽ* በውኃ ተበርዟል።

23 አለቆችሽ ግትሮችና የሌባ ግብረ አበሮች ናቸው።+

ሁሉም ጉቦ የሚወዱና እጅ መንሻ የሚያሳድዱ ናቸው።+

አባት የሌለው ልጅ ፍትሕ እንዲያገኝ* አያደርጉም፤

የመበለቲቱም አቤቱታ ወደ እነሱ አይደርስም።+

24 ስለዚህ እውነተኛው ጌታ፣ የሠራዊት ጌታ ይሖዋ፣

የእስራኤል ኃያል አምላክ እንዲህ ይላል፦

“እንግዲያው ስሙ! ባላጋራዎቼን አጠፋለሁ፤

ጠላቶቼንም እበቀላለሁ።+

25 እጄን በአንቺ ላይ አነሳለሁ፤

በመርዝ የማጥራት ያህል ቆሻሻሽን አቅልጬ አወጣለሁ፤

ዝቃጭሽንም ሁሉ አስወግዳለሁ።+

26 መጀመሪያ ላይ እንደነበረው ፈራጆችሽን፣

እንደቀድሞውም አማካሪዎችሽን መልሼ አመጣለሁ።+

ከዚያ በኋላ የጽድቅ መዲና፣ የታመነች ከተማ ተብለሽ ትጠሪያለሽ።+

27 ጽዮን በፍትሕ፣

የሚመለሱት ነዋሪዎቿም በጽድቅ ይቤዣሉ።+

28 ዓመፀኞችና ኃጢአተኞች በአንድ ላይ ይደቅቃሉ፤+

ይሖዋን የሚተዉም ያከትምላቸዋል።+

29 እናንተ በተመኛችኋቸው ግዙፍ ዛፎች ያፍራሉና፤+

በመረጣችኋቸው የአትክልት ቦታዎች* የተነሳም ትዋረዳላችሁ።+

30 ቅጠሉ እንደጠወለገ ትልቅ ዛፍ፣+

ውኃም እንደሌለው የአትክልት ቦታ ትሆናላችሁና።

31 ብርቱውም ሰው እንደ ተልባ እግር* ይሆናል፤

የሥራውም ውጤት እንደ እሳት ብልጭታ ይሆናል፤

ሁለቱም አብረው ይቃጠላሉ፤

እሳቱንም ማጥፋት የሚችል ማንም የለም።”

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ