የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኢሳይያስ 41
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ኢሳይያስ የመጽሐፉ ይዘት

      • ከፀሐይ መውጫ የመጣ ድል አድራጊ (1-7)

      • እስራኤል የአምላክ አገልጋይ እንዲሆን ተመረጠ (8-20)

        • ‘ወዳጄ አብርሃም’ (8)

      • ለአማልክት የቀረበ ፈተና (21-29)

ኢሳይያስ 41:1

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “እናንተ ደሴቶች፣ በፊቴ ዝም በሉ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 41:21

ኢሳይያስ 41:2

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ከምሥራቅ።”

  • *

    እሱን እንዲያገለግል የጠራው ማለት ነው።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 45:1
  • +ኢሳ 44:28፤ 46:11፤ ራእይ 16:12

ኢሳይያስ 41:4

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 43:10፤ 44:6፤ 48:12፤ ራእይ 1:8
  • +ኢሳ 46:4፤ ሚል 3:6፤ ያዕ 1:17

ኢሳይያስ 41:7

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 44:12፤ 46:6

ኢሳይያስ 41:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘፀ 19:5, 6፤ ዘሌ 25:42
  • +ዘዳ 7:6፤ መዝ 33:12
  • +2ዜና 20:7፤ ያዕ 2:23

ኢሳይያስ 41:9

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 107:2, 3
  • +ኢሳ 43:10
  • +1ሳሙ 12:22፤ ኤር 33:25, 26

ኢሳይያስ 41:10

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 20:1፤ መዝ 46:1፤ ሮም 8:31
  • +ኢሳ 60:19, 20
  • +ዘዳ 33:27፤ መዝ 115:9

ኢሳይያስ 41:11

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 45:24
  • +ኢሳ 40:17፤ 60:12

ኢሳይያስ 41:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 54:17

ኢሳይያስ 41:13

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 33:29

ኢሳይያስ 41:14

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    አቅመ ቢስና ትንሽ መሆኑን ያመለክታል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 7:7
  • +ኢሳ 43:14፤ 47:4

ኢሳይያስ 41:15

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሚክ 4:13

ኢሳይያስ 41:16

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 25:9
  • +ኢሳ 12:6

ኢሳይያስ 41:17

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 28:48፤ አሞጽ 8:11
  • +ኢሳ 30:19፤ 55:1
  • +መዝ 94:14፤ ኢሳ 42:16፤ ዕብ 13:5

ኢሳይያስ 41:18

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 30:25
  • +ኢዩ 3:18
  • +መዝ 107:35

ኢሳይያስ 41:19

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    እስከ 15 ሜትር የሚደርስ ርዝመት ያለው ትልቅ ዛፍ ነው። ቅጠሎቹ ፈዘዝ ያለ አረንጓዴ ቀለም ያላቸው ሲሆን ቅርንጫፎቹ ደግሞ አመድማ መልክ አላቸው።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 32:14, 15፤ 60:21
  • +ኢሳ 51:3፤ 55:13

ኢሳይያስ 41:20

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ሕዝ 39:28

ኢሳይያስ 41:22

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ልብ እንድናደርግና።”

  • *

    ቃል በቃል “ስለ መጀመሪያዎቹ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 42:9፤ 46:9, 10፤ 48:5

ኢሳይያስ 41:23

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 44:6, 7
  • +ኤር 10:5

ኢሳይያስ 41:24

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 44:10፤ ኤር 10:14, 15
  • +ዘዳ 7:26፤ 27:15፤ መዝ 115:4, 8

ኢሳይያስ 41:25

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ከምሥራቅ።”

  • *

    ወይም “የበታች ገዢዎችን።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 44:28፤ 45:1፤ ኤር 51:28, 29
  • +ኢሳ 46:11፤ ራእይ 16:12
  • +ሚክ 7:10

ኢሳይያስ 41:26

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 43:9፤ 44:7፤ 45:21
  • +ዕን 2:18, 19

ኢሳይያስ 41:27

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 43:10
  • +ዕዝራ 1:1, 2፤ ኢሳ 40:9

ኢሳይያስ 41:29

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ሁሉም ሕልውና የሌላቸው ነገሮች።”

  • *

    ወይም “ቀልጠው የተሠሩት ሐውልቶቻቸው።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 115:4-8፤ ኢሳ 44:9፤ 1ቆሮ 8:4

ተዛማጅ ሐሳብ

ኢሳ. 41:1ኢሳ 41:21
ኢሳ. 41:2ኢሳ 45:1
ኢሳ. 41:2ኢሳ 44:28፤ 46:11፤ ራእይ 16:12
ኢሳ. 41:4ኢሳ 43:10፤ 44:6፤ 48:12፤ ራእይ 1:8
ኢሳ. 41:4ኢሳ 46:4፤ ሚል 3:6፤ ያዕ 1:17
ኢሳ. 41:7ኢሳ 44:12፤ 46:6
ኢሳ. 41:8ዘፀ 19:5, 6፤ ዘሌ 25:42
ኢሳ. 41:8ዘዳ 7:6፤ መዝ 33:12
ኢሳ. 41:82ዜና 20:7፤ ያዕ 2:23
ኢሳ. 41:9መዝ 107:2, 3
ኢሳ. 41:9ኢሳ 43:10
ኢሳ. 41:91ሳሙ 12:22፤ ኤር 33:25, 26
ኢሳ. 41:10ዘዳ 20:1፤ መዝ 46:1፤ ሮም 8:31
ኢሳ. 41:10ኢሳ 60:19, 20
ኢሳ. 41:10ዘዳ 33:27፤ መዝ 115:9
ኢሳ. 41:11ኢሳ 45:24
ኢሳ. 41:11ኢሳ 40:17፤ 60:12
ኢሳ. 41:12ኢሳ 54:17
ኢሳ. 41:13ዘዳ 33:29
ኢሳ. 41:14ዘዳ 7:7
ኢሳ. 41:14ኢሳ 43:14፤ 47:4
ኢሳ. 41:15ሚክ 4:13
ኢሳ. 41:16ኢሳ 25:9
ኢሳ. 41:16ኢሳ 12:6
ኢሳ. 41:17ዘዳ 28:48፤ አሞጽ 8:11
ኢሳ. 41:17ኢሳ 30:19፤ 55:1
ኢሳ. 41:17መዝ 94:14፤ ኢሳ 42:16፤ ዕብ 13:5
ኢሳ. 41:18ኢሳ 30:25
ኢሳ. 41:18ኢዩ 3:18
ኢሳ. 41:18መዝ 107:35
ኢሳ. 41:19ኢሳ 32:14, 15፤ 60:21
ኢሳ. 41:19ኢሳ 51:3፤ 55:13
ኢሳ. 41:20ሕዝ 39:28
ኢሳ. 41:22ኢሳ 42:9፤ 46:9, 10፤ 48:5
ኢሳ. 41:23ኢሳ 44:6, 7
ኢሳ. 41:23ኤር 10:5
ኢሳ. 41:24ኢሳ 44:10፤ ኤር 10:14, 15
ኢሳ. 41:24ዘዳ 7:26፤ 27:15፤ መዝ 115:4, 8
ኢሳ. 41:25ኢሳ 44:28፤ 45:1፤ ኤር 51:28, 29
ኢሳ. 41:25ኢሳ 46:11፤ ራእይ 16:12
ኢሳ. 41:25ሚክ 7:10
ኢሳ. 41:26ኢሳ 43:9፤ 44:7፤ 45:21
ኢሳ. 41:26ዕን 2:18, 19
ኢሳ. 41:27ኢሳ 43:10
ኢሳ. 41:27ዕዝራ 1:1, 2፤ ኢሳ 40:9
ኢሳ. 41:29መዝ 115:4-8፤ ኢሳ 44:9፤ 1ቆሮ 8:4
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
  • 16
  • 17
  • 18
  • 19
  • 20
  • 21
  • 22
  • 23
  • 24
  • 25
  • 26
  • 27
  • 28
  • 29
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ኢሳይያስ 41:1-29

ኢሳይያስ

41 “እናንተ ደሴቶች፣ ዝም ብላችሁ አዳምጡኝ፤*

ብሔራትም ኃይላቸውን ያድሱ።

በመጀመሪያ ይቅረቡ፤ ከዚያም ይናገሩ።+

ለፍርድ አንድ ላይ እንሰብሰብ።

 2 ብሔራትን አሳልፎ ይሰጠውና

ነገሥታትን ድል ይነሳ ዘንድ+

ከፀሐይ መውጫ* አንዱን ያስነሳው፣+

በጽድቅ ወደ እግሩ የጠራው* ማን ነው?

በሰይፉ ፊት አቧራ የሚያደርጋቸው፣

በቀስቱ ፊት በነፋስ እንደተወሰደ ገለባ የሚያደርጋቸው ማን ነው?

 3 እግሩ ባልረገጠው መንገድ በመጓዝ

ምንም ነገር ሳያግደው እነሱን ያሳድዳል።

 4 ይህን የሠራና ያደረገ፣

ትውልዶቹንም ከመጀመሪያ አንስቶ የጠራ ማን ነው?

እኔ ይሖዋ የመጀመሪያው ነኝ፤+

ከመጨረሻዎቹም ጋር እኔ ያው ነኝ።”+

 5 ደሴቶች አይተው ፈሩ።

የምድር ዳርቻዎች ተንቀጠቀጡ።

ቀረቡ፤ ወደ ፊትም መጡ።

 6 እያንዳንዱም ባልንጀራውን ይረዳል፤

ወንድሙንም “አይዞህ፣ በርታ” ይለዋል።

 7 የእጅ ጥበብ ባለሙያውም አንጥረኛውን ያበረታታል፤+

በመዶሻ ብረቱን የሚያሳሳው

በመስፍ ላይ የሚቀጠቅጠውን ያበረታታዋል።

ብየዳውን በተመለከተ “ጥሩ ነው” ይላል።

ከዚያም ጣዖቱ እንዳይወድቅ አንድ ሰው በምስማር ይቸነክረዋል።

 8 “እስራኤል ሆይ፣ አንተ ግን አገልጋዬ ነህ፤+

ያዕቆብ ሆይ፣ አንተን መርጬሃለሁ፤+

የወዳጄ የአብርሃም ዘር ነህ፤+

 9 አንተን ከምድር ዳርቻዎች ወሰድኩህ፤+

እጅግ ርቀው ከሚገኙ ቦታዎችም ጠራሁህ።

እንዲህ ብዬሃለሁ፦ ‘አንተ አገልጋዬ ነህ፤+

እኔ መርጬሃለሁ፤ ገሸሽ አላደረግኩህም።+

10 እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ።+

እኔ አምላክህ ነኝና አትጨነቅ።+

አበረታሃለሁ፤ አዎ እረዳሃለሁ፤+

በጽድቅ ቀኝ እጄ አጥብቄ እይዝሃለሁ።’

11 እነሆ፣ በአንተ ላይ የተቆጡ ሁሉ ያፍራሉ፤ ይዋረዳሉም።+

ከአንተ ጋር የሚጣሉ ሁሉ እንዳልነበሩ ይሆናሉ፤ ይጠፋሉም።+

12 ከአንተ ጋር የሚፋለሙትን ሰዎች ትፈልጋቸዋለህ፤ ሆኖም አታገኛቸውም፤

ከአንተ ጋር የሚዋጉ ሰዎች እንደሌሉና ፈጽሞ እንዳልነበሩ ያህል ይሆናሉ።+

13 ‘አትፍራ። እረዳሃለሁ’ የምልህ

እኔ፣ አምላክህ ይሖዋ ቀኝ እጅህን ይዣለሁና።+

14 ትል* የሆንከው አንተ ያዕቆብ አትፍራ፤+

እናንተ የእስራኤል ሰዎች፣ እረዳችኋለሁ” ይላል የሚቤዥህ+ የእስራኤል ቅዱስ ይሖዋ።

15 “እነሆ፣ ማሄጃ፣ በሁለቱም በኩል የተሳሉ ጥርሶች ያሉት

አዲስ የመውቂያ መሣሪያ አድርጌሃለሁ።+

አንተም ተራሮቹን ረግጠህ ታደቃቸዋለህ፤

ኮረብቶቹንም እንደ ገለባ ታደርጋቸዋለህ።

16 ወደ ላይ ትበትናቸዋለህ፤

ነፋስም ይወስዳቸዋል፤

አውሎ ነፋስ ይበትናቸዋል።

በይሖዋ ደስ ይልሃል፤+

በእስራኤልም ቅዱስ ትኮራለህ።”+

17 “ችግረኞችና ድሆች ውኃ ይፈልጋሉ፤ ሆኖም አያገኙም።

ከመጠማታቸው የተነሳ ምላሳቸው ደርቋል።+

እኔ ይሖዋ እመልስላቸዋለሁ።+

እኔ የእስራኤል አምላክ አልተዋቸውም።+

18 በተራቆቱ ኮረብቶች ላይ ወንዞች እንዲፈስሱ አደርጋለሁ፤+

በሸለቋማ ሜዳዎች መካከል ምንጮችን አፈልቃለሁ።+

ምድረ በዳውን ቄጠማ የሞላበት ኩሬ፣

ውኃ የሌለበትንም ምድር የውኃ ምንጭ አደርጋለሁ።+

19 በበረሃ አርዘ ሊባኖስ፣

ግራር፣ አደስና ዘይት የሚሰጥ ዛፍ እተክላለሁ።+

በበረሃማ ሜዳ የጥድ ዛፍ፣

የአሽ ዛፍና* የፈረንጅ ጥድ በአንድነት እተክላለሁ፤+

20 ይህም የሚሆነው የይሖዋ እጅ ይህን እንዳደረገና

የእስራኤል ቅዱስ ይህን እንደፈጠረ

ሰዎች ሁሉ እንዲያዩና እንዲያውቁ፣

ልብ እንዲሉና በጥልቅ እንዲያስተውሉ ነው።”+

21 “ሙግታችሁን አቅርቡ” ይላል ይሖዋ።

“የመከራከሪያ ሐሳባችሁን አሰሙ” ይላል የያዕቆብ ንጉሥ።

22 “ማስረጃ አቅርቡ፤ እንዲሁም ወደፊት የሚሆኑትን ነገሮች ንገሩን።

በጥሞና እንድናስብባቸውና* ፍጻሜያቸውን እንድናውቅ

ስለቀድሞዎቹ* ነገሮች ንገሩን።

ወይም የሚመጡትን ነገሮች አሳውቁን።+

23 አማልክት መሆናችሁን እንድናውቅ

ወደፊት የሚሆነውን ነገር ንገሩን።+

አዎ፣ አይተን በአድናቆት እንድንዋጥ

መልካምም ሆነ ክፉ፣ የሆነ ነገር አድርጉ።+

24 እነሆ፣ እናንተ ጨርሶ ሕልውና የሌላችሁ ናችሁ፤

ምንም የምታከናውኑት ነገር የለም።+

እናንተን የሚመርጥ ሁሉ አስጸያፊ ነው።+

25 አንዱን ከሰሜን አስነስቻለሁ፤ እሱም ይመጣል፤+

የሚመጣው ከፀሐይ መውጫ*+ ሲሆን ስሜንም ይጠራል።

ጭቃውን እንደሚረግጥ ሸክላ ሠሪ

ገዢዎችን* እንደ ሸክላ አፈር ይረግጣቸዋል።+

26 እኛ እናውቅ ዘንድ ስለዚህ ነገር ከመጀመሪያው የተናገረ

ወይም ‘እሱ ትክክል ነው’ እንድንል ከጥንት ጀምሮ የተናገረ ማን ነው?+

በእርግጥ የተናገረ የለም!

ያሳወቀም የለም!

ከእናንተ አንዳች ነገር የሰማ የለም!”+

27 ከማንም በፊት ጽዮንን “ወደፊት የሚሆነውን ነገር ተመልከቺ!” ያልኩት እኔ ነኝ፤+

ለኢየሩሳሌምም ምሥራች ነጋሪ እልካለሁ።+

28 ሆኖም እኔ መመልከቴን ቀጠልኩ፤ አንድም ሰው አልነበረም፤

ከእነሱ መካከል ምክር የሚሰጥ አልነበረም።

እኔም መልስ እንዲሰጡ መጠየቄን ቀጠልኩ።

29 እነሆ፣ ሁሉም ቅዠት* ናቸው።

ሥራቸው ከንቱ ነው።

ከብረት የተሠሩት ምስሎቻቸው* ነፋስና መና ናቸው።+

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ