የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
  • ኢሳይያስ 47
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ

በዚህ ክፍል ውስጥ ምንም ቪዲዮ አይገኝም።

ይቅርታ፣ ቪዲዮውን ማጫወት አልተቻለም።

ኢሳይያስ የመጽሐፉ ይዘት

      • የባቢሎን መውደቅ (1-15)

        • ኮከብ ቆጣሪዎች ተጋለጡ (13-15)

ኢሳይያስ 47:1

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +መዝ 137:8፤ ኤር 50:41, 42
  • +ዳን 5:30

ኢሳይያስ 47:3

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    “ለማንም አልራራም” ማለትም ሊሆን ይችላል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዘዳ 32:35, 41፤ መዝ 94:1

ኢሳይያስ 47:4

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 41:14፤ 43:3፤ 44:6

ኢሳይያስ 47:5

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ንግሥት።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኢሳ 47:1
  • +ኢሳ 13:19፤ 14:4፤ ራእይ 17:5

ኢሳይያስ 47:6

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +2ዜና 36:15, 16፤ ኢሳ 42:24, 25፤ ዘካ 1:15
  • +ዘዳ 28:63፤ ሕዝ 24:21
  • +ኤር 52:14
  • +2ነገ 25:18-21፤ መዝ 137:8
  • +ዘዳ 28:49, 50

ኢሳይያስ 47:7

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ንግሥት።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዳን 4:30፤ ራእይ 18:7

ኢሳይያስ 47:8

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ራእይ 18:3
  • +ዳን 5:22, 23
  • +ራእይ 18:7

ኢሳይያስ 47:9

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    “መተት ብታበዢና ታላቅ ኃይል ያለው ድግምት ብትደግሚም” ማለትም ሊሆን ይችላል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ራእይ 18:10
  • +ሕዝ 21:21፤ ዳን 5:7፤ ራእይ 18:23
  • +ኤር 51:29

ኢሳይያስ 47:11

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “በድግምት እንዴት እንደምታርቂውም አታውቂም።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ራእይ 18:10

ኢሳይያስ 47:12

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዳን 2:2

ኢሳይያስ 47:13

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    “ሰማያትን የሚከፋፍሉ፤ ኮከብ ቆጣሪዎች” ማለትም ሊሆን ይችላል።

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ዳን 5:7

ኢሳይያስ 47:14

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ወይም “ነፍሳቸውን።”

ኢሳይያስ 47:15

የግርጌ ማስታወሻዎች

  • *

    ቃል በቃል “ወደየአካባቢያቸው ለመመለስ ይባዝናሉ።”

የኅዳግ ማጣቀሻዎች

  • +ኤር 51:6

ተዛማጅ ሐሳብ

ኢሳ. 47:1መዝ 137:8፤ ኤር 50:41, 42
ኢሳ. 47:1ዳን 5:30
ኢሳ. 47:3ዘዳ 32:35, 41፤ መዝ 94:1
ኢሳ. 47:4ኢሳ 41:14፤ 43:3፤ 44:6
ኢሳ. 47:5ኢሳ 47:1
ኢሳ. 47:5ኢሳ 13:19፤ 14:4፤ ራእይ 17:5
ኢሳ. 47:62ዜና 36:15, 16፤ ኢሳ 42:24, 25፤ ዘካ 1:15
ኢሳ. 47:6ዘዳ 28:63፤ ሕዝ 24:21
ኢሳ. 47:6ኤር 52:14
ኢሳ. 47:62ነገ 25:18-21፤ መዝ 137:8
ኢሳ. 47:6ዘዳ 28:49, 50
ኢሳ. 47:7ዳን 4:30፤ ራእይ 18:7
ኢሳ. 47:8ራእይ 18:3
ኢሳ. 47:8ዳን 5:22, 23
ኢሳ. 47:8ራእይ 18:7
ኢሳ. 47:9ራእይ 18:10
ኢሳ. 47:9ሕዝ 21:21፤ ዳን 5:7፤ ራእይ 18:23
ኢሳ. 47:9ኤር 51:29
ኢሳ. 47:11ራእይ 18:10
ኢሳ. 47:12ዳን 2:2
ኢሳ. 47:13ዳን 5:7
ኢሳ. 47:15ኤር 51:6
  • አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
  • 1
  • 2
  • 3
  • 4
  • 5
  • 6
  • 7
  • 8
  • 9
  • 10
  • 11
  • 12
  • 13
  • 14
  • 15
አዲስ ዓለም ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
ኢሳይያስ 47:1-15

ኢሳይያስ

47 አንቺ ድንግል የባቢሎን ሴት ልጅ ሆይ፣+

ወርደሽ አፈር ላይ ተቀመጪ።

አንቺ የከለዳውያን ሴት ልጅ ሆይ፣

ዙፋን በሌለበት መሬት ላይ ተቀመጪ፤+

ከእንግዲህ ሰዎች ቅምጥልና ሞልቃቃ ብለው አይጠሩሽምና።

 2 ወፍጮ ወስደሽ እህል ፍጪ።

መሸፋፈኛሽን አንሺ።

ቀሚስሽን አውልቂ፤ ባትሽን ግለጪ።

ወንዞቹን ተሻገሪ።

 3 እርቃንሽ ይገለጣል።

ኀፍረትሽም ይታያል።

እኔ የበቀል እርምጃ እወስዳለሁ፤+ ማንም ሰው ሊያግደኝ አይችልም።*

 4 “እኛን የሚቤዠን

የእስራኤል ቅዱስ ነው፤+

ስሙም የሠራዊት ጌታ ይሖዋ ነው።”

 5 አንቺ የከለዳውያን ሴት ልጅ ሆይ፣

በዚያ ዝም ብለሽ ተቀመጪ፤ ወደ ጨለማም ግቢ፤+

ከእንግዲህ የመንግሥታት እመቤት* ብለው አይጠሩሽም።+

 6 ሕዝቤን ተቆጣሁ።+

ርስቴን አረከስኩ፤+

አሳልፌም በእጅሽ ሰጠኋቸው።+

አንቺ ግን ምሕረት አላሳየሻቸውም።+

በሽማግሌው ላይ እንኳ ሳይቀር ከባድ ቀንበር ጫንሽ።+

 7 አንቺም “ሁልጊዜ ብሎም ለዘላለም እመቤት* እሆናለሁ” አልሽ።+

እነዚህን ነገሮች ልብ አላልሽም፤

ነገሩ ምን ፍጻሜ እንደሚኖረው አላሰብሽም።

 8 በመሆኑም አንቺ ለሥጋዊ ደስታ ያደርሽ፣+

ተማምነሽ የተቀመጥሽና

በልብሽ “እኔ ነኝ፤ ከእኔም በቀር ሌላ የለም።+

መበለት አልሆንም።

በምንም ዓይነት የወላድ መሃን አልሆንም” የምትዪ ሴት ሆይ፣+ ይህን ስሚ።

 9 ሆኖም እነዚህ ሁለት ነገሮች ይኸውም

የወላድ መሃንነትና መበለትነት በአንድ ቀን በድንገት ይደርሱብሻል።+

በመተት ስለተሞላሽና ታላቅ ኃይል ባለው ድግምት ስለተዘፈቅሽ*+

እነዚህ ነገሮች ሁሉ በአንቺ ላይ ይደርሳሉ።+

10 አንቺ በክፋትሽ ታምነሻል።

“ማንም አያየኝም” ብለሻል።

ያሳቱሽ ጥበብሽና እውቀትሽ ናቸው፤

በልብሽም “እኔ ነኝ፤ ከእኔም በቀር ሌላ የለም” ትያለሽ።

11 ሆኖም ጥፋት ይመጣብሻል፤

ደግሞም ከዚህ ሊያስጥልሽ የሚችል ድግምት የለሽም።*

መከራ ይደርስብሻል፤ ልታስወግጂውም አትችዪም።

አይተሽው የማታውቂው ጥፋት በድንገት ይደርስብሻል።+

12 እንግዲያው ከልጅነትሽ ጀምሮ ስትደክሚበት የነበረውን

ድግምት ሁሉና ብዛት ያለው የጥንቆላ ድርጊት+ መፈጸምሽን ቀጥዪ።

ምናልባት ይጠቅምሽ ይሆናል፤

ሰዎችን ለማሸበር ይረዳሽ ይሆናል።

13 በመካሪዎችሽ ብዛት እጅግ ተዳክመሻል።

በሰማያት ያሉ ነገሮችን የሚያመልኩ፣* ከዋክብትን በትኩረት የሚመለከቱ፣+

አዲስ ጨረቃም ስትወጣ

በአንቺ ላይ ስለሚመጣው ነገር የሚተነብዩ ሰዎች፣

እስቲ አሁን ተነስተው ያድኑሽ።

14 እነሆ፣ እነሱ እንደ ገለባ ናቸው።

እሳት ያቃጥላቸዋል።

ራሳቸውን* ከነበልባሉ ኃይል ማዳን አይችሉም።

ይህ ሰዎች የሚሞቁት ፍምም ሆነ

በፊቱ ተቀምጠው የሚሞቁት እሳት አይደለም።

15 ከልጅነትሽ ጀምሮ አብረሻቸው ስትደክሚ የነበሩት

ድግምተኞች እንዲሁ ይሆኑብሻል።

እያንዳንዳቸው የመረጡትን አቅጣጫ ተከትለው ይባዝናሉ።*

አንቺን የሚያድን አይኖርም።+

የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ ጽሑፎች (2011-2025)
ውጣ
ግባ
  • የኢትዮጵያ ምልክት ቋንቋ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ